Popular Posts

Saturday, October 20, 2018

በእግዚአብሄር ላይ የምንደገፍባቸው አምስት የህይወታችን ክፍሎች


ሰው በእግዚአብሄር የተፈጠረው በእግዚአብሄር በራሱ ላይ ተደግፎ እንዲኖር ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሄር ላይ እንዲደገፍ ዲዛይን ስለተደረገ ከእግዚአብሄር ነፃ መውጣት በፈለገ መጠን ሁሉ ለዚያ ስላልተሰራ አይሳካለትም፡፡ ሰው ግን ራሱን ትሁት አድጎ በእግዚአብሄር ላይ በተደገፈ መጠን ይከናወንለታል ይሳካለታል ህይወትንም ያያል፡፡ ሰው የህይወትን ጣእም የሚቀምሰው በእግዚአብሄር ላይ ብቻ ሲደገፍ ነው፡፡  
በእግዚአብሄር ላይ ከምንደገፍባቸው ዋና ዋና የህይወት ክፍላችን በጥቂቱ እንመልከት
ለእኛ የተለየ አላማ እንዳለው በእግዚአብሄር እንታመናለን
የተፈጠረንው በድንገት አይደለም፡፡ የተፈጠርነው በአላማ ነው፡፡ ህይወታችንን ከጥፋት የሚጠብቀውና ስኬት ውስጥ የሚያስገባን አንድ ነገር ስለ ህይወት አላማችን በእግዚአብሄር ላይ መደገፍ ነው፡፡ እኛ ራሳችንን አልፈጠርንም፡፡ እግዚአብሄር የህይወታችን ፈጣሪና ባለቤት ነው፡፡ እኛ የራሳችን አይደለንም፡፡ እኛ ብንረሳው እንኳን በህይወታችን ያለውን አላማ እግዚአብሄር አይረሳውም፡፡ እኛ ባይገባን እንኳን የህይወታችን ያለውን አላማ እግዚአብሄር እስኪፈፅመው ድርስ አያርፍም፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን ያለውን አላማ ለመፈጸፀም እስከፈለግን ድረስ የእግዚአብሄርን አላማ አንስተውም፡፡ እግዚአብሄር በህይወቱ ያለውን አላማ መፈፀም የሚፈልግ ሰው ከእግዚአብሄር ጋር አይተላለፍም፡፡ የእግዚአብሄር አላማ በህይወቱ እንዲፈፀም ራሱን የሰጠ ሰው አላማውን አይስተውም፡፡
ፈቃዱን ሊያደርግ የሚወድ ቢኖር፥ እርሱ ይህ ትምህርት ከእግዚአብሔር ቢሆን ወይም እኔ ከራሴ የምናገር ብሆን ያውቃል። የዮሐንስ ወንጌል 7፡17
እግዚአብሄር የሚያስፈልገን እንደሚያሟላ በእግዚአብሄር እንታመናለን  
እግዚአብሄርን የምናምነው በእኛ ላይ ታላቅ የህይወት አላ እንዳለው ብቻ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር ለህይወታችን የሚያስፈክገው ነገር ሁሉ እንደሚሰጠን እንታመነዋለን፡፡ በራሳችን እግዚአብሄርን ማገልገል የምንችል ቢሆን ኖሮ አግዚአብሄር አያስፈልገንም ነበር፡፡ እግዚአብሄርን የምንከተለውና የምናገለግለው በእርሱ ወጪ ነው፡፡
የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። 2 የጴጥሮስ መልእክት 1፡2-3
እግዚአብሄር እንደሚጠብቀን በእግዚአብሄር እንታመናለን
እግዚአብሄር ሁሉን እንደሚያውቅና በምናልፍበት ነገር ውስጥ ሁሉ እንደሚጠብቀን በእግዚአብሄር እንታመናለናለን፡፡   
እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም። እግዚአብሔር ይጠብቅሃል፥ እግዚአብሔርም በቀኝ እጅህ በኩል ይጋርድሃል። ፀሐይ በቀን አያቃጥልህም ጨረቃም በሌሊት። እግዚአብሔር ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል፥ ነፍስህንም ይጠብቃታል። ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እግዚአብሔር መውጣትህና መግባትህን ይጠብቃል። መዝሙረ ዳዊት 121፡4-8
ብንስት እንደሚመልሰን በእግዚአብሄር እንታመናለን 
እኛ ሁሉን አናውቅም፡፡ እግዙአብሄር ግን ስለ እኛ ሁሉን ያውቃል፡፡ እግዚአብሄር እንዳንሰት የጠብቀናል፡፡ እግዚአብሄር ብንስት እንኳን ይገስፀናል ይመልሰናል፡፡ ብንስት እግዚአብሄር ይቅር ይለናል፡፡ እግዚአብሄር ሁለተኛ እድልን ይሰጠናል፡፡
በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1፡9
ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ። መዝሙረ ዳዊት 23፡3
ፀጋውን እንደሚያበዛልን በእግዚአብሄር እንታመናለን
እግዚአብሄርን እንድንኖርለት የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ እንደሚሰጠን በእግዚአብሄር ላይ እንደገፋለን፡፡ በእርሱ በሚያስችል ሃይል እና ፀጋ እግዚአብሄርን ለማስደሰት እንደምንችል እናምናለን፡፡ እግዚአብሄር የሰጠን ፀጋ በቂ እንደሆነና እግዚአብሄርን በአካሄዳችን እንደምናረካውና እንደምናስደስተው በእግዚአብሄር አሰራር እንታመናለን፡፡
እኛ ሁላችን ከሙላቱ ተቀብለን በጸጋ ላይ ጸጋ ተሰጥቶናልና ሕግ በሙሴ ተሰጥቶ ነበርና፤ ጸጋና እውነት ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ሆነ። የዮሐንስ ወንጌል 1፡16-17
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መደገፍ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መታመን #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment