Popular Posts

Friday, October 19, 2018

ተስፋ መቁረጥ


በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፤ በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፤ እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፤ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም፤ 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 4፡8-9
ተስፋ መቁረጥ የህይወት ፈተና ነው፡፡ ተስፋ መቁረጥ እንደ ሙሴ አይነቶቹን አገልጋዮች ፈትኗል፡፡
እጅግ ከብዶኛልና ይህን ሁሉ ሕዝብ ልሸከም አልችልም። እንዲህስ ከምታደርግብኝ፥ በፊትህ ሞገስ አግኝቼ እንደ ሆነ፥ በእኔ ላይ የሚሆነውን መከራ እንዳላይ፥ እባክህ፥ ፈጽሞ ግደለኝ። ኦሪት ዘኍልቍ 11፡14-15
ተስፋ መቁረጥ አነደኤልያስ ያሉትን ታላቅ ነቢያት ተፈታትኗል፡፡
ኤልያስም ፈርቶ ተነሣ፥ ነፍሱንም ሊያድን ሄደ፥ በይሁዳም ወዳለው ወደ ቤርሳቤህ መጥቶ ብላቴናውን በዚያ ተወ። እርሱም አንድ ቀን የሚያህል መንገድ በምድረ በዳ ሄደ፤ መጥቶም ከክትክታ ዛፍ በታች ተቀመጠና፦ ይበቃኛል አሁንም፥ አቤቱ፥ እኔ ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ ብሎ እንዲሞት ለመነ። መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ 19፡3-4
ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ ለመተውና እጅ ለመስጠት የማይፈተን ሰው ካለ በህይወት የለማይኖር የሞተ ሰው ብቻ ነው፡፡ አቁም የሚል ተስፋ የሚያስቆርጥ ብዙ ድምፅ ባለበት ሁኔታ ውስጥ ተስፋ የማንቆርጥባቸው ከአልጋችን ላይ መነሳት በማይሰማን ጊዜ ለጌታ እንደገና በሃይል ለጌታ ለመኖርና በአዲስ ጉልበት ጌታን ለማገልገል አስፈንጥርው ከአልጋችን የሚያስነሱን አምስት ዋና ዋና ምክኒያቶች፡  
1.      መቼም እጅ የማንሰጠው በህይወታችን ከእኛ በላይ የሆነ የእግዚአብሄር አላማ ስላለ ነው፡፡
ራሳችንን ብቻ ብናይ ተስፋ እንቆርጣለን፡፡ በአካባቢያችን ባለው ነገር ላይ ብቻ ብናተኩር ተስፋ ለመቁረጥ ይቀለናል፡፡ ነገር ግን ከራሳችን በላይ የምናያው ለአላማው የፈጠረን እግዚአብሄር አለ፡፡ ከሁኔታችን ባሻገር የምንመለከተው በምድር ላይ ልንፈፅመው የተወለድነለት የእግዚአብሄር አላማ አለ፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን ያስቀመጠውን ሃላፊነት እኛ ካልሰራነው ማንም ሊሰራው አይችልም የሚል ሸክም አለን፡፡
ጲላጦስም፦ እንግዲያ ንጉሥ ነህን? አለው። ኢየሱስም መልሶ፦ እኔ ንጉሥ እንደ ሆንሁ አንተ ትላለህ። እኔ ለእውነት ልመሰክር ስለዚህ ተወልጃለሁ ስለዚህም ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ከእውነት የሆነ ሁሉ ድምፄን ይሰማል አለው። የዮሐንስ ወንጌል 18፡37
2.     ለምንም እጅ የማንሰጠው በህይወታችን የምንሰራው ነገር በዘላለማዊ እይታ ትርጕም ስላለው ነው፡፡
በህይወታችን የምንኖረው ለምድራዊው ነገር ብቻ ቢሆን ተስፋ መቁረጥ ቀላል ነበር፡፡ ነገር ግን ከምድር ህይወት በኋላ ህይወት እንዳለ በክርስቶስ ፍርድ ፊት እንደምንቀርብ ስለምናውቅ ተስፋ መቁረጥ አይታሰብም፡፡ የምድር ኑሮ አጭር እንደሆነ እና እኛ በህይወት ከቆየን ክርስቶስ ተመልሶ እንደሚመጣና እንደሚወስድን ስለምናውቅ ተስፋ እንቆርጥም፡፡  
ወዳጆች ሆይ፥ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን፥ ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። ዳሩ ግን ቢገለጥ እርሱ እንዳለ እናየዋለንና እርሱን እንድንመስል እናውቃለን። በእርሱም ይህን ተስፋ የሚያደርግ ሁሉ እርሱ ንጹሕ እንደ ሆነ ራሱን ያነጻል። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 3፡2-3
3.     በህይወታችን የምንሰራው ለትውልድ የሚሆን መሰረት ስለሆነ ነው
ህይወታችን በእኛ የሚያልቅ ቢሆን ተስፋ መቁረጥ ይቀል ነበር፡፡ ነገራቸን ከመቃብር ባሻገር የማይዘልቅ ቢሆን ተስፋ ለመቁረጥ ፊት በሰጠነው ነበር፡፡ ነገር ግን እኛን የሚመለከቱ እኛ ምሳሌ የምንሆናቸው ጌታ እንዲከተሉና እንዲያገለግሉ ብርታት የምንሆናቸው የሚመጣ ትውልድ ምሳሌ መሆን ስላለብን ስለራሳችን ብቻ ሳይሆን ስለመጪው ትውልድ እናስባለን እንጠነቀቃለን፡፡ የእኛ ተስፋ መቁረጥ እኛ ላይ ብቻ ሳይሆን በሚመጣው ትውልድ ላይ ሁሉ ያለውን ተፅእኖ ስለምንረዳ እጅ አንሰጥም፡፡
እናንተ ጽድቅን የምትከተሉ እግዚአብሔርንም የምትሹ፥ ስሙኝ፤ ከእርሱ የተቈረጣችሁበትን ድንጋይ ከእርሱም የተቈፈራችሁበትን ጕድጓድ ተመልከቱ። ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም፥ ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሳራ ተመልከቱ፤ አንድ ብቻውን በሆነ ጊዜ ጠራሁት፥ ባረክሁትም አበዛሁትም። ትንቢተ ኢሳይያስ 51፡1-2
በአንተ ያለውን ግብዝነት የሌለበትን እምነትህን አስባለሁ፤ ይህም እምነት ቀድሞ በአያትህ በሎይድ በእናትህም በኤውንቄ ነበረባቸው፥ በአንተም ደግሞ እንዳለ ተረድቼአለሁ። 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1፡5
አንተ ግን ትምህርቴንና አካሄዴን አሳቤንም እምነቴንም ትዕግሥቴንም ፍቅሬንም መጽናቴንም ስደቴንም መከራዬንም ተከተልህ፤ 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3፡10
4.     በህይወታችን የምንሰራው ነገር ሽልማት ስላለው ነው
እግዚአብሄርን ተስፋ ያደረግነው ለዚህ ኑሮ ብቻ ቢሆን ተስፋ መቁረጥ ቀላል ይሆን ነበር፡፡ ነገር ግን ተስፋ አለመቁረጣችን ዋጋ አለው፡፡ ተስፋ አለመቁረጣችን ታላቅ ብድራት ያስገኛል፡፡
የሚበልጥና ለዘወትር የሚኖር ገንዘብ በሰማይ ራሳችሁ እንዳላችሁ አውቃችሁ፥ በእስራቴ ራራችሁልኝ የገንዘባችሁንም ንጥቂያ በደስታ ተቀበላችሁ። እንግዲህ ታላቅ ብድራት ያለውን ድፍረታችሁን አትጣሉ። ወደ ዕብራውያን 10፡34-35
5.     ተስፋ የማንቆርጠው በህይወት የምንፈልገው ነገር ባይሆንም እግዚአብሄር የሚፈልገው ነገር እየሆነ ስለሆነ ነው፡፡
በሆነው ባልሆነው እጅ የማንሰጠው እኛ ባይመቸንም እግዚአብሄር አላማውን እየፈፀመ ስለሆነ ነው፡፡ እኛን ደስ ባይለንም የእግዚአብሄር አሰራር ስራውን እየፈፀመ ስለሆነ ነው፡፡ የተለያዩ ነገር ቢያስጨንቀንም እንኳን ለመልካም ስለሚሆን ነው፡፡
እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን። ወደ ሮሜ ሰዎች 8፡28
የውጭው ሰውነት ቢጠፋ ዋናው የውስጡ ሰውነት እለት እለት እየታደሰ ስለሆነ ነው፡፡
ስለዚህም አንታክትም፥ ነገር ግን የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳ የውስጡ ሰውነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል። የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 4፡16-18
ለእነርሱም እግዚአብሔር በአሕዛብ ዘንድ ያለው የዚህ ምሥጢር ክብር ባለ ጠግነት ምን እንደ ሆነ ሊያስታውቅ ወደደ፥ ምሥጢሩም የክብር ተስፋ ያለው ክርስቶስ በእናንተ ዘንድ መሆኑ ነው። ወደ ቆላስይስ ሰዎች 1፡27
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ  Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ክብር #መዋረድ #መከራ #ፈተና #ሞት #በሁሉ #እንገፋለን #አንጨነቅም #እናመነታለን #ተስፋአንቆርጥም #እንሰደዳለን #አንጣልም #እንወድቃለን #አንጠፋም #ህይወት #ስጋ #መፅናት #መታገስ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ብፅእና #እምነት #አንድነት #ፀጋ  #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment