Popular Posts

Monday, October 22, 2018

ታማኝነት ሲፈተን


እግዚአብሄር ሊያሳድገን ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር በተሻለ ነገር ላይ ሊሾመን ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር አሁን ካለንበት የተሻለ ነገር አለው፡፡ እግዚአብሄር ለተሻለ ነገር አጭቶናል፡፡
ታማኝነት አግዚአብሄር ከሰጠን ሃላፊነት በምንም ምክኒያት ወደኋላ አለማለት ነው፡፡ ታማኝነት እግዚአብሄር የሰጠንን ስጦታ እንደ ባለአደራ እርሱ እንደፈለገው መጠቀም ነው፡፡ ታማኝነት ቢመችም ባይመችም እግዚአብሄርን በትህትና ማገልገል ነው፡፡ ታማኝነት ለፈተና እጅ ሳይሰጡ እና ከመንገድ ሳያቋርጡ ጉዞን መፈፀም ነው፡፡ ታማኝነት እግዚአብሄር እስከሚናገረን ድረስ በሁኔታዎች ቦታችንን አለመልቀቅ ነው፡፡
ነገር ግን እግዚአብሄር እኛን ለተሻለ ነገር ሲያጨን ለዚያ ሃላፊነት ከመሾሙ በፊት ለከፍታው እንደምንመጥን ማወቅ ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ከመሾሙ በፊር ለቦታው እንደምንስማማ አቅማችንን ማየት ይፈልጋል፡፡  
የሚሆንልን ነገር ልንሸከመው ከምችልው በላይ ሆኖ እንዲያስጨንቀን እግዚአብሄር አይፈልግም፡፡ የምናገኘው ነገር ከአቅማችን በላይ ሆኖ እኛንም ይዞን እንዲጠፋ እግዚአብሄር ይጠነቀቃል፡፡
ስለዚህ እግዚአብሄር ከማሳደጉ በፊት መፈተን ይፈልጋል፡፡ በተለያየ ነገር ሳይፈትን የሚያሳድገው ሰው የለም፡፡
እነዚህም ደግሞ አስቀድሞ ይፈተኑ፥ ከዚያም በኋላ ያለ ነቀፋ ቢሆኑ በዲቁና ሥራ ያገልግሉ። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3፡10
እግዚአብሄር ስለምንደርስበት ቦታ የሚፈትነን አሁን ባለንበት ነገር ነው፡፡ እግዚአብሄር ስለምናገኘው ነገር አያያዝ የሚፈትነን አሁን ያለንን ነገር በምንይዘበት አያያዝ ነው፡፡ እግዚአብሄር ስለምንነሆነው ነገር የሚፈትነን በሆንነው ነገር ነው፡፡
ከሁሉ በሚያንስ የታመነ በብዙ ደግሞ የታመነ ነው፥ ከሁሉ በሚያንስም የሚያምፅ በብዙ ደግሞ ዓመፀኛ ነው። የሉቃስ ወንጌል 16፡10
በትንንሽ ሃላፊነቶች ተፈትነን ካለፍን በታላላቅ ሃላፊነቶች ይባርከናል፡፡
ጌታውም፦ መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። የማቴዎስ ወንጌል 25፡21
በትንንሽ ሃላፊነት ካለታመንን ግን ለትልቅ ሃላፊነት አንታመንም፡፡ በትንንሽ ሃላፊነቶች ካልታመንን ያለን ሃላፊነት እንኳን ይወሰዳል፡፡
ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፥ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር። ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አሥር መክሊትም ላለው ስጡት፤ የማቴዎስ ወንጌል 25፡27-28
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #ታማኝ #የታመነ #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መደገፍ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መታመን #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment