Popular Posts

Tuesday, February 21, 2017

የእምነት ብቸኛው መንገድ

በአይን ከማይታየው መንፈስ ከሆነው ከእግዚአብሄር ጋር ላለን ግንኙነት እምነት በጣም ወሳኝ ነው፡፡ እግዚአብሄርን ለመድረስና ከእግዚአብሄር ለመቀበል የእምነት እጅ ይጠይቃል፡፡ እግዚአብሄርን ለማየት የእምነት እይታ ይጠይቃል፡፡ በአጠቃላይ እግዚአብሄርን ለማስደሰትና ከእግዚአብሄር ጋር ያለው ግንኙነታችን እንዲሰምር እምነት ይጠይቃል፡፡ እንዲያውም ካለእምነት እግዚአብሄርን ማስደሰት አይቻልም፡፡
ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ዕብራውያን 11፡6
ታዲያ እምነትን የምናገኘው እንዴት ነው? እምነት እንዴት ይመጣል? የሚለውን ጥያቄ መመለስ ብልህነት ነው፡፡
ከእግዚአብሄር ፈቃድ ውጭ እምነት የማይታሰብ ነው፡፡ እምነት ይኖረን ዘንድ መጀመሪያ ስለ ሁኔታችን የእግዚአብሄር ቃል የሚለውን ማግኘት ግዴታ ነው፡፡ እምነት የሚገኘው የእግዚአብሄር ፈቃድ ሲገኝ ብቻ ነው፡፡ እምነት የሚመጣው በእግዚአብሄር ቃል መረዳት ብቻ ነው፡፡
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ሮሜ 10፡17
ከእምነት ጉዞ የሚቀድመው ዋንኛው ነገር የእግዚአብሄርን ፈቃድ ከቃሉ ፈልጎ ማግኘት ነው፡፡ እምነት የሚያመጣውን ቃሉን መስማትና መረዳት ነው፡፡
በእምነት ለመኖር በእግዚአብሄር ቃል መኖር አለብን፡፡ እግዚአብሄርን ለመስማትና ለማመን ቃሉን መስማት አለብን፡፡  
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment