Popular Posts

Saturday, February 25, 2017

ፍቅር 100 %

ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው፥ አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ማርቆስ 12፡29-30
እግዚአብሄር የዘላለም ንጉስ ነው፡፡ እግዚአብሄር ከእኛ ግማሽ ወይም የተከፋፈለ ፍቅር አይቀበልም፡፡ እግዚአብሄር ከእኛ ሙሉ ፍቅር ይጠብቃል፡፡ እገዚአብሄር ኩሩ ነው እግዚአብሄር ጎዶሎን ነገር እንዳውም አይቀበለም፡፡
ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው። ያዕቆብ 1፡7-8
እኛ የእግዚአብሄር ፍጥረት ነን፡፡ ለክብሩ የሰራን ፍጥረቶቹ ነን፡፡ ሲፈጥረን ለምን እንደፈጠረን ሊናገር የሚችለው እርሱ ብቻ ነው፡፡ በእኛ ላይ ሙሉ ስልጣን ያለውና ከእኛ ምን እንደሚፈልግ በሙሉ ስልጣን ማዘዝ የሚችለው እግዚአብሄር ነው፡፡
ይህ ለክብሩ የፈጠረን ጌታ ከእኛ የሚጠብቀው 100% እንድንወደ ነው፡፡
በፍፁም ልባችን እንድንወደው እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡ ልብ የህይወታችን ማእከላዊ ስፍራና የህይወት ሁሉ ምንጭ ነው፡፡ እግዚአብሄር ከልባችን እንድንወደው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ከትርፋችን ሳይሆን ከዋናችን እንድንወደው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄርን ከላይ ከላይ ሳይሆን ከውስጣችን እንድንወደው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄርን በአንደበታችን ሳይሆን ከልባችን እንድንወደቅው ይፈልጋል፡፡ እገዚአብሄር ለታይታ ሳይሆን በፍፁም እንድወደው ይፈልጋል፡፡  
ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል፥ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤ ማቴዎስ 15፡8
እግዚአብሄር በፍፁም ነፍሳችን እንድንወደው ይጠብቅብናል፡፡ እግዚአብሄር በሙሉ ስሜታቸን እንድንናስቀድመው ይፈልጋል፡፡ ስለእርሱ ስናስብ ልባችን እንዲሞቅ ይፈልጋል፡፡ ስለእርሱ ስንናገር ልባችን እንዲቀጣጠል ይፈልጋል፡፡ እርሱን ስናገልግል በደስታና በፈንጠዝያ እንድናገለግለው ይጠብቃል፡፡ እግዚአብሄር በሙሉ ልባችን እንድንወደው ይፈልጋል፡፡
እግዚአብሄር በፍፁም ሃሳባችን እንድንወደውም ይፈልጋል፡፡ ሃሳባችን በርሱ ሃሳብ እንዲሞላ ይፈልጋል፡፡ በህይወታችን ተግዳሮት ሲያጋጥመን የመጀመሪያው የመፍትሄ ሃሳብ የእርሱ እንዲሆን ይፈልጋል፡፡ ምንም ከመወሰናችን በፊት እርሱን አስበን እንድንወስን ይፈልጋል፡፡ በህይወታችን የእርሱን ሃሳብ ከሌላ  ሃሳብ በፊት እንድናስቀድመው ይፈልጋል፡፡
እግዚአብሄር በፍፁም ሃይላችን እንድንወደው ይፈልጋል፡፡ ባለን ጉልበት ሁሉ እንድናስደስተው ፣ ባለን ጉልበት ሁሉ እንድንከተለው ፣ ባለን ጉልበት ሁሉ ካለምንም ቁጠባና መሰሰት ለእርሱ እንድንኖርለት ይፈልጋል፡፡
ይህን ስናነብ "ይህ ይቻላል?" ብለን ልንጠይቅ እንችላለን፡፡ መልሱ ይቻላል ነው፡፡ እግዚአብሄር ካዘዘው ይቻላል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር ከጠየቀው ይቻላል ማለት ነው ምክኒያቱም እግዚአብሄር የማይቻል ነገር ለአፉ ጠይቆ አያውቅም፡፡  
ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው፥ አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ማርቆስ 12፡29-30
 ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ፍቅር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #በፍፁምልብ #በፍፁምሃሳብ #በፍፁምነፍስ #በፍፁምሃይል #መውደድ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment