Popular Posts

Monday, February 27, 2017

የሰመጠው ጓደኛ ታሪክ

ዎች ማን ኒ የተባሉ ቻይናዊ አገልጋይ The Normal Christian Life በአማርኛ (ክርስትና እንዲህ ነው) ተብሎ በተተረጎመው መፅሃፋቸው ላይ እኛ አማኞች በመንፈስ ቅዱስ ላይ እንዴት መደገፍ አንዳለብን ሲያስተምሩ ይህንን ታሪክ ፅፈዋል፡፡
በድሮ ዘመን  የምንታጠብበት የተዘጋጀ ቦታ ስላልነበረን ሰውነታችንን የምንታጠበው ወንዝ ወርደን ነበር፡፡ እንደተለመደው አንድ ጊዜ ወንዝ ወርደን እየታጠብን እያለ አንዱ ዋና የማይችል ጓደኛችን ውሃ ውስጥ ገባ፡፡ ዋና ባለመቻሉ ለመዳን ባለው መፍጨርጨር ምክኒያት ብቅ ጥልቅ ይል ጀመር፡፡ አንድ በመካከላችን ዋና የሚችል ጓደኛችን ነበርና ገብተህ አውጣው ብለን መጮኽ ጀመርን ፡፡ ነገር ግን ጥያቄያችን ዋና የሚችለውን ጓደኛችንን ብዙም ሊያንቀሳቅሰው አልቻለም፡፡ በዚህም ምክኒያት ቶሎ ወደ ውሃው በመግባት ሊያወጣው አልሞከረም ነበር፡፡ ጓደኛችን ቆየት ብሎ ግን ውሃ ውስጥ ገብቶ ጓደኛችንን አወጣው፡፡
በጣም ተገርመን ለምንድነው ግን መጀመሪያ ወደውሃ ውስጥ ገብተህ ለመርዳት ያልሞከርከው ለሚለው ጥያቄያችን መልሱ ይህ ነበር፡፡ ልክ ውሃ ውስጥ አንደወደቀ እኔም ወደውሃው ብገባ ኖሮ እሱ ብቻ ሳይሆን ሁላችንም እንሰጥም ነበር፡፡ ምክኒያቱም እርሱ በሙሉ ሃይሉ ነበር የነበረው፡፡ ለመዳን በሚያደርገው መፍጨርጨር አንገቴ ላይ ተጠምጥሞ ይደፍቀኝና ይገድለኝ ነበር፡፡
ስለዚህ ነው ትንሽ መጠበቅ የፈለግኩት፡፡   ከትንሽ ጊዜ በኋላ በራሱ ሞክሮ ሲያቅተውና እየደከመ ሲመጣ በትንሽ ሃይል ገፍቼ አወጣዋለሁ ብዬ ነው፡፡ እርሱም ጉልበቱን በመፍጨርጨርና በመሞከር ስለቀነሰ እኔንም ሊገድለኝ የማይችለብት ድካም ላይ ነበር የነበረው ብሎ አስረዳን፡፡
እንዲሁም በህይወታችን የሚያስፈልገን ነገር በራሳችን ጉልበት መፍጨርጨር ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ ላይት ማረፍና መደገፍ ነው፡፡ እኛ በራሳችን ጉልበት ለማድረግ ስንሞክርና ስንፍጨረጨር እግዚአብሄር ያርፋል፡፡ እኛ በእርሱ ላይ ስናርፍ ፣ ለእርሱ እሺ ስንልና ራሳችንን በእርሱ ላይ ስንተው እርሱ በእኛ ይሰራል፡፡  
በመንፈስ ብንኖር በመንፈስ ደግሞ እንመላለስ። ገላትያ 5፡25
በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው የሕይወት መንፈስ ሕግ ከኃጢአትና ከሞት ሕግ አርነት አውጥቶኛልና። ሮሜ ሰዎች 8፡1-2
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #መንፈስቅዱስ #አፅናኝ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መሰጠት #መገዛት #ምሪት #ድምፅ #ቅባት #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መውደድ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment