Popular Posts

Tuesday, December 6, 2016

መዝገብህ ባለበት ልብህ

ልብህ የሚሄደው መዝገብህ ባለበት ቦታ ነው፡፡ ሰው በተፈጥሮው ሃብቱና ልቡ ተነጣጠለው አይኖሩም፡፡ መዝገብህ ባለበት ልብህ በዚያ ይሆናል፡፡
መዝገብህ በሌለበት ቦታ ልብህ በዚያ አይኖርም፡፡ ትኩረትህ ሁሉ የሚኖረው የኔ የምትለው የምትጠነቀቅለት ነገር ባለበት ቦታ ነው፡፡ ስለዚህ አለ ኢየሱስ ልባችሁ በሰማይ እንዲያተኩር ወሳኙ መንገድ ፣ ልባችሁ በሰማይ እንዲቀር የሚረዳው ነገር ፣ ልባችሁ በሰማይ ትኩረት እንዲያዝ ከፈለጋችሁ መዝገባችሁን በሰማይ አስቀምጡ እያለን ነው፡፡
በምድር ላይ የምንደገፍበት ነገር ሲጠፋ ልባችን ወደ ሰማይ መዝገብ ያዘነብላል፡፡ ነገር ግን የምድር ሃብታችን ሲበዛና በዚያም ለመታመን ስንፈተን ልባችንም በምድር ላይ ይቀራል፡፡ ልባችንን የምንጥልበት ሃብታችን በምድር ላይ እየበዛ በሄደ መጠን ልባችን ከሰማይ ላይ እየተነሳ ይሄዳል፡፡ መዝገባችን በምድር ሲሆን ልባችንም በምድር ይሆናል፡፡ መዝገባችን በሰማይ ሲሆን በቅፅበት ልባችንም በሰማይ ይሆናል፡፡
ብዙ ጊዜ ልባችን ከሰማይ በመነሳት እንፈተናልን፡፡ በዚህ ፈተና ያለመውደቅ መንገዱን ኢየሱስ ያስተምራል፡፡ መዝገብን በምድር የመሰብሰብ ጉዳቱ ልባችንን ከሰማይ ላይ እንዲነሳ ሰማይ ትኩረታችን እንዳይሆን ያደርጋል፡፡ መዝገብን በሰማይ የመሰብሰብ ጥቅሙ ልባችንን በሰማይ ይሰበስብልናል፡፡
ብልና ዝገት በሚያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በሚሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በምድር ላይ መዝገብ አትሰብስቡ፤ ነገር ግን ብልም ዝገትም በማያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በማይሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፤ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና። ማቴዎስ 6፡19-21
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መዝገብ #ሃብት #ሰማይ #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ጥሪ #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment