Popular Posts

Sunday, December 11, 2016

ዓመቱ ሲመዝን

ክርስትያን በየጊዜው ህይወቱን በእግዚአብሄር ቃል መመዘን አለበት፡፡ በየጊዜው የማይገመገምና የማይፈተሽ ህይወት ከንቱ ህይወት ነው፡፡
ሃዋሪያው የእግዚአብሄርን ስራ ለረጅም ጊዜ ከሰራ በኋላ ተመልሶ በከንቱ ሮጬ እንዳይሆን በማለት ህይወቱን ሲመዝን እናያለን፡፡  
ፈትኖ መልካም እንዲሆን በሚቈጥረው ነገር በራሱ ላይ የማይፈርድ ብፁዕ ነው። ሮሜ 14፡22
ሰዎች በትክክል ህይወታቸውን መመዘን ካልቻሉ ስህተታቸውን ማስተካከል አይችሉም፡፡ ሰዎች እንዴት ህይወታቸውን ከጊዜ ወደጊዜ መመዘን እንዳለባቸው ካላወቁ ለተሻለም ስራ አይነሱም፡፡ ሰዎች ህይወታቸውን በትክክል መመዘን ካልቻሉ ደስታቸውን ያጣሉ፡፡ ሰዎች በትክክል ህየወታቸውን ካልመዘኑ እግዚአብሄር በውስጣው ባስቀመጠው በጎነት እግዚአብሄርን ፈፅመው ማክበር አይችሉም፡፡
ህይወታችንን ግን እንዴት ነው የምንመዝነው፡፡
በክርስትና ህይወታችንን የምንመዝንበት መንገድ ታማኝነታችንን በመመዘን ብቻ ነው፡፡ ከታማኝነት ውጭ ራሳችንን ለመመዘን የምንችልበት ትክክለፃ መመዘኛ አናገፅም፡፡   
ታማኝነት የህይወታችን ብቸኛው መለኪያ ነው፡፡ ሰው ታማኝነቱ የሚታየው ባለው ፣ እግዚአብሄር በሰጠውና በእጁ ባለው ነገር ነው ፡፡ እግዚአብሄር የሚጠይቀን የሰጠንን መክሊት እንዴት እንደተጠቀምንበት ነው፡፡
·         ታማኝነታችን የሚለካው ባለን እወቀት ነው፡፡ 
ታማኝነታችን የሚለካው በሆነ እውቀት ሳይሆን ባለን እውቀት በተሰጠን እውቀት ምን ያህል ታማኝ መሆናችን ነው፡፡
የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ባሪያ እጅግ ይገረፋል፤ ያላወቀ ግን መገረፍ የሚገባውንም ያደረገ ጥቂት ይገረፋል። ብዙም ከተሰጠው ሰው ሁሉ ከእርሱ ብዙ ይፈለግበታል፥ ብዙ አደራም ከተሰጠው ከእርሱ አብዝተው ይሹበታል። ሉቃስ 12፡47-48
·         ታማኝነታችን የሚለካው እግዚአብሄር በሰጠን ጊዜ ነው፡፡ 
እግዚአብሄር የሰጠኝን ጊዜ በትክክል ለእግዚአብሄር ክብር አውዬዋለሁ፡፡ እግዚአብሄር የሰጠኝን ጊዜ ቃሉን ለማንበብ በሚገባ ተጠቅሜበታለሁ፡፡ እግዚአብሄር የሰጠኝን ጊዜ ጌታን ለማምለክ ተጠቅሜበታለሁ? እግዚአብሄር የሰጠኝን ጊዜ ፊቱን ለመፈለግ ተጠቅሜበታለሁ?   
·         ታማኝነታችን የሚለካው በሃይል አስተዳደራችን ነው፡፡ 
እግዚአብሄር የሰጠንን ሃይልና ችሎታ ለክፉ ነገር ላለመጠቀም መወሰናችን ታማኞች ያደርገናል፡፡ እግዚአብሄር የሰጠንን ሃይል ግን በጥላቻና በመለያየት ላይ ካጠፋነው በታማኝነት አልተመላለስንም፡፡ 
·         ታማኝነታችን የሚለካው እግዚአብሄር በሰጠን ገንዘብ ነው፡፡
እግዚአብሄር ለመብላት የሰጠንን መብላታችን እግዚአብሄር ለመዝራት የሰጠንን በመዝራታችን ታማኝነታችን ይለካል፡፡
·         ታማኝነታችን የሚለካው የተሰጠንን መክሊት አጠቃቀማችን ነው፡፡
ታማኝነታችን የሚለካው እግዚአብሄር የሰጠንን መንፈሳዊ ስጦታን ለቤተክርስቲያን ጥቅምና ለእግዚአብሄር ክብር እንዴት በታማኝነት እንደተጠቀምንበት ነው፡፡  
አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ። ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው። ማቴዎስ 25፡18-19
·         ታማኝነት የሚለካው በተሰጠን ተፅእኖ ነው፡፡
ታማኝነታችን የሚለካው በተሰጠን የተሰጠንን ተሰሚነት ለእግዚአብሄ ክብር ወይም ለራሳችን ጥቅም መጠቀማችን ነው፡፡
ጌታውም፦ መልካም፥ አንተ በጎ፥ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፥ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። ማቴዎስ 25፡23
ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ የተባለው ባሪያ ለተሻለ ሃላፊነት ይሾማል፡፡ አስተውላችሁ እንደሆነ የጠየቃቸው ያልሰጣቸውንም ሳይሆን የሰጣቸውን አንዴት በታማኝነት እንዳስተዳደሩት ብቻ ነው፡፡ የምንመዝነው ታማኝነታችንን ብቻ ነው፡፡ ታማኝ ከነበርን ፈተናውን አልፈናልና ደስ ሊለን ይገባል፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ታማኝ #ትጉህ #መክሊት #ትውልድ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ሃሳብ #ገንዘብ #ጊዜ #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment