Popular Posts

Friday, December 23, 2016

ኢየሱስ ብቻ አይደለም የተወለደው !

ለብዙ ሰዎች የኢየሱስ መወለድ ከእለታት አንድ ቀን የተፈፀመ ታሪክ ብቻ ነው፡ ለእነዚህ ሰዎች የኢየሱስ መሞት በህይወታቸው ያመጣው ምንም ነገር የለም፡፡ በኢየሱስ መወለድ ህይወታቸው አልተለወጠም፡፡ በኢየሱስ መወለድ ህይወታቸው የተወለደ ነገር የለም፡፡
ኢየሱስ በቤተልሄም እንደተወለደ በህይወታችን ሊወለድና ሊኖር ይገባዋል፡፡
ኢየሱስ የተወለደው ታሪክ ሊሰራ አይደለም፡፡ ኢየሱስ የተወለደው ለገድል አይደለም፡፡
ኢየሱስ የተወለደው ለእውነት ሊመሰክር ነው፡፡
እውነትን መፈለግ አቁመናል፡፡ በኢየሱስ እውነትን አግኝተነዋል፡፡
ጲላጦስም፦ እንግዲያ ንጉሥ ነህን? አለው። ኢየሱስም መልሶ፦ እኔ ንጉሥ እንደ ሆንሁ አንተ ትላለህ። እኔ ለእውነት ልመሰክር ስለዚህ ተወልጃለሁ ስለዚህም ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ዮሃንስ 18፡37
ኢየሱስ የተወለደው ለዓለም ብርሃን ሊሆን ነው፡፡
ዓለም በጨለማ በተያዘበት ጊዜ ወዴት እንደሚሄድ ምን እንደሚያደናቅፈው ባለወቀ ጊዜ ኢያስ በጨለማ የሚያበራ ብርሃን ሆኖ መጣ፡፡  
በእኔ የሚያምን ሁሉ በጨለማ እንዳይኖር እኔ ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ። ዮሃንስ 12፡46
ደግሞም ኢየሱስ፦ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው። ዮሃንስ 8፡12
ኢየሱስ የተወለደው በመስቀል ላይ ሊሞት ነው፡፡
ኢየሱስ የተወለደው እኛ ከእግዚአብሄር እንድንወለድ ነው፡፡ ኢየሱስ የተወለደው እኛ ወደ እግዚአብሄር ቤተሰብ ውስጥ አንድንገባ ነው፡፡ ኢየሱስ የተወለደው እኛ የእግዚአብሄር የቤተሰብ አባላት የመሆን ስልጣን እንድናገኝ ነው፡፡
የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ዮሃንስ 1፡11-12
ኢየሱስ የተወለደው ከሃጢያት ሊያድነን ነው
ከሃጢያት ካልዳንን ኢየሱስ የተወለደበትን አላማ ስተነዋል ማለት ነው፡፡ ከሃጢያት ሃይል ነፃ ካልወጣን የኢየሱስ መሞት ታሪክ ብቻ ነው ማለት ነው፡፡  
ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ። ማቴዎስ 1፡21
ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ሉቃስ 2፡11
ኢየሱስ የተወለደው ሰላምን ሊሰጠን ነው
በምንም ምድራዊ ሁኔታ የማይለዋወጥ እውነተኛ ሰላም ፣ ምንም ነገር የማያደፈርሰው ሰላም ከሌለን ኢየሱስ የተወለደበትን አላማ ተጠቃሚ አልሆንም ማለት ነው፡፡
ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። . . . እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ፦ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ። ሉቃስ 2፡11-14
ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም። ዮሐንስ 14፡27
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ወልድ #ልጅ #አዳኝ #መድሃኒት #ሰላም #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ብርሃን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መንገድ #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment