Popular Posts

Friday, December 16, 2016

ሁሉ የእናንተ ነው

1 ቆሮንቶስ 3:21 ሁሉ የእናንተ ነው፡፡
·         የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ
እግዚአብሄር ለኢየሱስ የሰጠውን ክብር ኢየሱስ ለእኛ ሰጥቶናል፡፡ ይህንንም ክብር የሰጠን ኢየሱስ እና አብ አንድ እንደሆኑ እኛም በኢየሱስ አንድ እንድንሆን ነው፡፡   
እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ ዮሐንስ 17፡22
·         መንግሥትን ሊሰጣችሁ የአባታችሁ በጎ ፈቃድ ነውና
አንተ ታናሽ መንጋ፥ መንግሥትን ሊሰጣችሁ የአባታችሁ በጎ ፈቃድ ነውና አትፍሩ። ሉቃስ 12፡32
·         ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን
በህይወት ጌታን ለመከተልና እግዚአብሄር በህይወታችን ያዘጋጀውን መልካሙን ስራ ጨርሰን እንድናከብረው የሚያስፈልገው ወጭ ሁሉ ተሰጥቶናል፡፡  
የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። 2ኛ ጴጥሮስ 1፡2-3
·         እግዚአብሄር እረኛችን ነው
መልካም ነገር የሚባል ነገር ሁሉ ተሰጥቶናል፡፡ የሚያስፈልገን ነገር ሁሉ ተሰጥቶናል፡፡ መልካም ከሚባል ነገር አንጎድልም፡፡
እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። መዝሙር 1፡23
. . . እግዚአብሔርን የሚፈልጉት ግን ከመልካም ነገር ሁሉ አይጐድሉም። መዝሙር 34፡10
·         መግባት የእኛ ነው፡፡
እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ በመረቀልን በአዲስና በሕያው መንገድ ወደ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት በሥጋው በኩል እንድንገባ ድፍረት ስላለን፥ ዕብራውያን 10፡19-20
·         ንግስና የእኛ ነው
በአንዱም በደል ሞት በአንዱ በኩል ከነገሠ፥ ይልቁን የጸጋን ብዛትና የጽድቅን ስጦታ ብዛት የሚቀበሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሕይወት ይነግሣሉ። ሮሜ 5፡17
·         በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው
እግዚአብሄር አብ ኢየሱስን በሚወደው መጠን ይወደናል፡፡
እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል። ዮሐንስ 17፡23
ነገር ሁሉ የእናንተ ነውና፤ ጳውሎስ ቢሆን አጵሎስም ቢሆን ኬፋም ቢሆን ዓለምም ቢሆን ሕይወትም ቢሆን ሞትም ቢሆን ያለውም ቢሆን የሚመጣውም ቢሆን፥ ሁሉ የእናንተ ነው፥ እናንተም የክርስቶስ ናችሁ ክርስቶስም የእግዚአብሔር ነው። 1ኛ ቆሮንቶስ 3፡21-23
ይህ ሁሉ የሚሆነው ግን ለሁሉም ሰው አይደለም፡፡ ሁሉ የእናንተ ነው የተባሉት ኢየሱስን የህይወታቸው አዳኝና ጌታ አርገው  የተቀበሉትን ብቻ ነው፡፡
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ዮሃንስ 1፡12
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ሁሉየእናንተነውና #መንግስት #ፍቅር #እረኛእግዚአብሄር #ክርስቶስ #የሚያስፈልገውን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ብርሃን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  #የዋህነት #ንፁህ

No comments:

Post a Comment