Popular Posts

Saturday, December 3, 2016

የህይወት ጥያቄ መልስ

ጥበብ ዓይነተኛ ነገር ናትና ጥበብን አግኝ፤ ከሀብትህም ሁሉ ማስተዋልን አትርፍ። ምሳሌ 4፡7
በህይወታችን ያሉትን ጥያቄዎች ሁሉ ገንዘብ ሊመልሳቸው የሚችል ይመስለናል፡፡ ስለዚህ ትኩረታችን ከአስፈላጊው ነገር ላይ ተነስቶ ወደ አላስፈላጊው ነገር ላይ ይሆናል፡፡ አብዛኛው የህይወታችን ጥያቄ የሚመለሰው ተጨማሪ ገንዘብ ስናገኝ ሳይሆን ባለን ነገር እንዴት መኖር እንደምንችል ጥበብ ስናገኝ ነው፡፡ ከእኛ ያነሰ ገንዘብ ኖሮዋቸው ከእኛ የተሻለ የሚኖሩ ሰዎች አሉ፡፡ ለህይወት ስኬት ሁሌ ተጨማሪ ገንዘብ በፈለግን ቁጥር ህይወትን እንደሚገባው ማጣጣም አንችልም፡፡
በአብዛኛው ለህይወት ስኬት የሚጠቅመን ነገር ብዙ ገንዘብ ማከማቸት ሳይሆን ባለን ነገር ለመኖር ማስተዋልን ማግኘት ነው፡፡ አንዳንዳንዱ የህይወት ጥያቄው በገንዘብ እንጂ በሌላ በምንም ነገር እንደማይፈታ አእምሮውን የዘጋው ሰው ይህንን ንግግር አይታገሰውም፡፡
ጥበብ አይነተኛ ነገር ነች፡፡ ጥበብን የሚገባዋን ክብር ካልሰጠናትና ካልተከተልናት ጥበበኞች አንሆንም፡፡ ክጥበብና ከህይወት እንጎድላለን፡፡ የጠቢቡ ምክር ከሃብትህም በላይ ማስተዋልን አትርፍ ነው፡፡ ለሃብት ከጥበብ ያነሰ ክብር ስጠው፡፡ ሃብትን አጋንነህ የጥበብ ያህል እትፈልገው፡፡ ሃብትህን ብታጣ ይሻላል ጥበብን ከምታጣ፡፡ ሃብት ውስጥ ሁሉ ነገር የለም፡፡ ጥበብ ውስጥ ግን ሁሉ ነገር አለ፡፡
ብልጥግናና ክብር በእኔ ዘንድ ነው፥ ብዙ ሀብትና ጽድቅም። ፍሬዬም ከምዝምዝ ወርቅ ይሻላል፥ ቡቃያዬም ከተመረጠች ብር። ምሳሌ 8፡18-19
በህይወታችን ያለው ጥያቄ የገንዘብ ፣ የሃይልና የዝና ማነስ ሊመስለን ይችላል፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ ግን ገንዘቡም ሃይሉም ዝናውም የማያደርገውን ጥበብ ለነገስታት እንዲሚያደርገው ይናገራል፡፡ ጥበብ አይነተኛ ነገር ነው፡፡
ምክርና መልካም ጥበብ የእኔ ነው፤ ማስተዋል እኔ ነኝ፥ ብርታትም አለኝ። ነገሥታት በእኔ ይነግሣሉ፥ ሹማምቶችም የቀናውን ነገር ይደነግጋሉ። ምሳሌ 8፡14-15
መፅሃፍም ማንም በህይወት ሲፈተን ከፈተናው መውጫ ጥበብን ይለምን ነው እንጂ ገንዘብን አይደለም ይለምን አይደለም ያለው፡፡
ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፥ ለእርሱም ይሰጠዋል። ያዕቆብ 1፡5
ጥበብ አይነተኛ ነገር እንደሆነች ስንረዳ አብዛኛው የፀሎት ርእሳችን ይቀየራል፡፡ ጥበብ አይነተኛ ነገር እንደሆነች ከልባችን ስንረዳ ትኩረታችን በትክክለኛው ቦታ ላይ ይሆናል፡፡ ጥበብ አይነተኛ ነገር እንደሆነች ስንረዳ ባለንበት ደረጃ ህይወትን በሚገባ መኖር እንጀምራለን፡፡ ጥበብ አይነተኛ ነገር እንደሆነች ስንረዳ ለህይወት ጥያቄያችን መልስ የምንፈልገው ጥበብን ሊሰጠን የሚችለው መፅሃፍ ቅዱስ ጋር ይሆናል፡፡ ጥበብ አይነተኛ ነገር እንደሆነች ስንረዳ ለህይወት ጥያቄያችን ዘወር የምንለው በውስጣችን ወዳለው የጥበብ መንፈስ መንፈስ ቅዱስ ይሆናል፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes


#ኢየሱስ #ጌታ #ጥበብ #ማስተዋል #መረዳት #ቤተክርስትያን #መንፈስቅዱስ #ብርታት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment