Popular Posts

Tuesday, December 27, 2016

ህይወት እንደ ሲና ቡና

(Life is Like a cup of coffee) ከሚለው የተተረጎመ  
ከኮሌጅ የተመረቁና በስራቸውም ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱ ባለሙያዎች የድሮ የዩኒቨርሲቲ መምህር ፕሮፌሰራቸውን ለመጎብኘት በአንድነት ተሰበሰቡ፡፡ ውይይቱ በፍጥነት በስራና በህይወት ውጥረት ላይ ወደ ማጉረምረም ተለወጠ፡፡
ፕሮፌሰሩ ለእንግዶቹ ቡና ለማቅረብ ወደ ኩሽና ሄዶ አንድ ትልቅ ጀበና ቡናና አንዳንዱ ልሙጥ ፣ አንዳንዱ ውድአንዳንዱ የሚያምር ከሸክላ የተሰራ ሲኒ ፣ ከፕላስቲክ የተሰራ ሲኒ ፣ ከብርጭቆ የተሰራ ሲኒ ይዞላቸው መጣና ራሳቸውን አንዲያስተናግዱ ነገራቸው፡፡
ሁሉም ተማሪዎች አንድ አንድ ቡና ሲኒ እንደያዙ ፕሮፌሰሩ እንዲህ አለ: "አስተውላችሁ ከሆነ ርካሾቹና ልሙጦቹ ሲኒዎች ተትተው  የሚያምሩትና ውዶቹ ሁሉም ሲኒዎች ተወስደዋል፡፡ ለራሳችሁ ምርጥ ነገር መፈለጋችሁ የሚጠበቅ ቢሆንም የህይወታችሁ ውጥረትና ችግር ምንጭ ይኸው ነው፡፡
ሲኒው ለቡናው ጥራት ምንም አስተዋፅኦ አያደርግም፡፡ አንዳንዴ እንዳውም ብዙ ብር ያስወጣል፡፡ አንዳንዴም የምንጠጣውን ቡና ይደብቀዋል፡፡ ሁላችሁም በእርግጥ የሚያስፈልጋችሁ ቡናው እንጂ ሲኒው አይደለም፡፡ ነገር ግን አስባችሁ ምርጡን ሲኒ አነሳችሁ፡፡  ከዚያም በኋላ አንዳችሁ የሌላችሁን ሲኒ ማየት ጀመራችሁ፡፡
ተመልከቱ ሕይወት ቡናው ነው፡፡ በኅብረተሰቡ ውስጥ ያለን ስራ ፣ ገንዘብ እና የህይወት ደረጃ አቋም ሲኒዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሲኒዎች ሕይወትን የሚይዙ መያዣዎች እቃዎች እንጂ ህይወት አይደሉም፡፡ የምንጠጣበት ሲኒ ቡናውን ሊገልፀው አይችልም ወይም የምንኖረውን ህይወት ጥራት አይለውጠውም፡፡
አንዳንድ ጊዜ ሲኒው ላይ ብቻ በማተኮር በቡናው መደሰት ያቅተናል፡፡ ቡናውን አጣጥም እንጂ ሲኒውን አይደለም! 
እጅግ ደስተኛ ሰዎች ሁሉ ምርጥ ነገር ሁሉ የላቸውም፡፡ ነገር ግን ካላቸው ነገር ምርጥ ነገርን ማውጣት ይችላሉ፡፡
በቀላሉ ኑር ፣ በልግስ ውደድ ፣ ለሌላው በሚገባ አስብ በደግነት ተናገር፡፡
ኑሮዬ ይበቃኛል ለሚለው ግን እግዚአብሔርን መምሰል እጅግ ማትረፊያ ነው፤ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡6
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ራስንማማጠን #ደስተኝነት #ያለኝይበቃኛል #ህይወት #ዘላለም #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መንገድ #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment