Popular Posts

Friday, December 30, 2016

እግዚአብሄርን የማመስገን መልካምነት

እግዚአብሄርን ለማመስገን ብዙ ምክኒያቶች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ እግዚአብሄርን ለማመስገን የሁሉም ሰው የጋራ ምክኒያት የሆነው አንድ ምክኒያት ነው፡፡ ሰው ሌላ ምክኒያት ቢያጣ እንኳን በዚህ ምክኒያት እግዚአብሄርን ሊያመሰግን ይገባዋል፡፡ ሰው ምክኒያት ቢያጣ እንኳን ይህ ምክኒያት እግዚአብሄርን ለማመስገን በቂ ነው፡፡
መፅሃፍም ቅዱስም ይህን ምክኒያት እግዚአብሄርን ለማመስገን ምክኒያት አድርጎ ደጋግሞ ፅፎታል፡፡
እግዚአብሄር መልካም ነው፡፡ እግዚአብሄር ሁለንተናው መልካም ነው፡፡ እግዚአብሄር አይለወጥም ሁልጊዜም መልካም ነው፡፡
የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ አትሳቱ። በጎ ስጦታ ሁሉ ፍጹምም በረከት ሁሉ ከላይ ናቸው፥ መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ በመዞርም የተደረገ ጥላ በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ። ያዕቆብ 1፡16-17
የመልካምነት ትርጉሙ ቢያከራክር እንኳን ለመልስ እግዚአብሄርን ማየት በቂ ነው፡፡ እግዚአብሄር የመልካምነት ማጣቀሻ (Refrence) ነው፡፡ ሰው በሚያነበው መፅሃፍ ላይ ያለን ቃል ትርጉም ባይረዳ ማጣቀሻን ይፈልግና የቃሉን ትርጉም ያያል፡፡ እንደዚሁ የመልካምነት ትርጉሙ ቢያጠራጥር እግዚአብሄር ጋር መልሱ አይታጣም፡፡
እግዚአብሄር መልካም ብቻ ሳይሆን የመልካምነትም ደረጃ መዳቢ ነው፡፡ እሱ መልካም ያለው መልካም ነው እርሱ መልካም አይደለም ያለው መልካም አይደለም፡፡ ስለ መልካምነት የመጨረሻው ወሳኝ አካል እግዚአብሄር ነው፡፡ እግዚአብሄርን የሚያርመው የለም፡፡ እግዚአብሄርም ማንንም አያማክርም፡፡
እግዚአብሄርን መልካም ስለሆነና ምንም የማይወጣለት ፍፁም መልካም ስለሆነ እግዚአብሄርን ማመስገን መልካም ነው፡፡ ሰው በምንም ነገር ቢሳሳት እግዚአብሄርን ስለማመስገኑ በጭራሽ አይሳሳትም፡፡ እግዚአብሄርን ማመስገን ምንም የሚወጣለት ነገር የለም፡፡  
እግዚአብሄር መልካም ስለሆነ ምስጋና ይገባዋል፡፡ እግዚአብሄርን ማመስገን ይገባል፡፡ እግዚአብሄርን ማመስገን ውበት አለው፡፡ እግዚአብሄርን ማመስገን ያማረ ነው፡፡
እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ መዝሙር መልካም ነውና። ለአምላካችን ምስጋና ያማረ ነው። መዝሙር 147፡1
ሃሌ ሉያ። የእግዚአብሔርን ስም አመስግኑ፤ እናንተ የእግዚአብሔር ባሪያዎች ሆይ፥ አመስግኑት፥ እግዚአብሔር ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ለስሙ ዘምሩ፥ መልካም ነውና፤ መዝሙር 135፡1፣3
እግዚአብሔርን ማመስገን መልካም ነው፥ ልዑል ሆይ፥ ለስምህም ዝማሬ ማቅረብ፤ በማለዳ ምሕረትን፥ በሌሊትም እውነትህን ማውራት አሥር አውታር ባለው በበገና፥ ከምስጋና ጋርም በመሰንቆ። መዝሙር 92፡1-3
ሃሌ ሉያ። ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ መዝሙር 107፡1
ሃሌ ሉያ። እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ ቸር ነውና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ናትና። መዝሙር 118፡ 1
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #አመስግኑ #መልካም #እምነት #ቃልኪዳን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #አብርሃም #መንፈስ #መንፈስቅዱስ

No comments:

Post a Comment