Popular Posts

Friday, December 2, 2016

የሌለኝ የማያስፈልገኝ ነው

እግዚአብሄር ለአላማ ፈጥሮናል፡፡ የመፈጠራችን አላማ ደግሞ ከመኖር ያለፈ አላማ ነው፡፡ እግዚአብሄር የሰራን ለራሱ ነው፡፡ እግዚአብሄር የፈጠረን ለክብሩ ነው፡፡ እግዚአብሄር በምድር ላይ የሚያኖረን የእርሱን ክብሩንና በጎነቱን እንድናሳይለት ነው፡፡
ወደ ምድር የመጣነው ድንገት አይደለም፡፡ ወደ ምድር የመጣነው እግዚአብሄር ስለፈለገን ነው፡፡ እግዚአብሄር ክብሩን ሊገልጥብን እንድናገለግለው ለፈቃዱ እንድንኖር ወደ ምድር አምጥቶናል፡፡
እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን። ኤፌሶን 2፡10
ለመኖር የሚያስፈልገንን የማሟላት ሃላፊነት ያለበት እግዚአብሄር ሲሆን ለእግዚአብሄር ክብር የመኖር ሃላፊነት ያለብን ደግሞ እኛ ነን፡፡ የእኛ ሃላፊነት የእግዚአብሄን መንግስት ጥቅምና በጎነት መፈለግ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ሃላፊነት የሚያስገልገንን ሁሉ ማሟላት ነው፡፡
እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። ማቴዎስ 6፡31-33
ስለዚህ ነው ሐዋሪያው ጳውሎስ ለህይወት የሚያስፈልገንን ሁሉ እግዚአብሄር በክብር እንደሚሞላብን የሚያስተምረው፡፡ አምላኬም እንደ ባለ ጠግነቱ መጠን በክብር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ይሞላባችኋል። ፊልጵስዩስ 4፡19
ስለዚህ ነው መዝሙረኛው እረኛው እግዚአብሄር ስለሆነ ከሚያስገልገው ነገር አንዱንም እንደማያሳጣው የዘመረው፡፡ እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። መዝሙር 23፡1
አንድ የማከንብራቸው የእግዚአብሄር ሰው "የሌለኝ ነገር ሁሉ የሌለኝ ስለማያስፈልገኝ ነው" አሉ፡፡
እውነት ነው እግዚአብሄር እረኛችን ሆኖ የሌለን ነገር ካለ ቢያንስ ቢያንስ ለአሁን አያስፈልገንም ማለት ነው፡፡ ወደፊት የሚያስፈልገን ከሆነ እግዚአብሄር በጊዜው ውብ አድርጎ ሰርቶታል፡፡ ለአሁን ግን የሌለኝ ሁሉ የማያስፈልገኝ ነው፡፡ እግዚአብሄር ለእኛ መልካም የሚያደርግ ሆኖ መልካም ለማደርግ ሙሉ ችሎታ ኖሮት ሳለ የሌለን ነገር የማያስፈልገን ነው፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #እረኛ #አላማ #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ጥሪ #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment