Popular Posts

Tuesday, November 14, 2017

ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር

አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን። ዮሐንስ 1፡15
በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው በመልኩና በአምሳሉ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ለክብሩ ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሄ ክብር ነው የተፈጠረው፡፡ ሰው የእግዚአብሄር ክብር የጎደለው በሃጢያት ሲወድቅ ነው፡፡
ኢየሱስ የሃጢያታችንን እዳ ሁሉ በመስቀል ላይ በመክፈሉ ኢየሱስን የሚቀበል ሰው ሁሉ እግዚአብሄር ልጅ አድርጎ ይቀበለዋል፡፡
ኢየሱስን የተቀበለ ሰው ሁሉ የእግዚአብሄር ልጅ ነው፡፡
ግን የእግዚአብሄር ልጅ ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን ጥያቄ መመለስ ወሳኝ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ልጅነትን ክብር እስካላወቅን ድረስ የልጅነት ጥሪያችንን መረዳት አንችልም፡፡ የእግዚአብሄር ልጅነትን ክብር እስካልተረዳን ድረስ ልጆች ሆነን መመላለስ አንችልም፡፡ የእግዚአብሄር ልጅነትን ክብር እስካልተረዳን ድረስ በልጅነት መብትና ስልጣን መኖር ያቅተናል፡፡ የእግዚአብሄርን ልጅነት ክብር እስካልተረዳን ድረስ በእግዚአብሄር ልጅነት ደረጃ በመኖር እግዚአብሄር በህይወታችን ላይ ያለውን አላማ መፈፀም አንችልም፡፡
ልጅ ላልሆኑት የልጅነትን ክብር ሊያሳይ የሚችለ ልጅ የሆነ ብቻ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ልጅነት  ክብር የምናየው የእግዚአብሄር አንድያ ልጅ ከነበረው ከኢየሱስ ነው፡፡ አሁን ኢየሱስ የእግዚአብሄር አንድያል ልጅ አይደለም፡፡ በኢየሱስ የሚያምኑትን እግዚአብሄር ልጅ አድርጎ ስለተቀበላቸው እግዚአብሄር ብዙ ልጆች አሉት፡፡ አሁን ኢየሱስ የበኩር ልጅ ነው፡፡
ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ ዋጋ ለመክፈል ብቻ አይደለም፡፡ ኢየሱስ ወደምድር የመጣው የሃጢያታቸውን መስዋእት ኢየሱስን የተቀበሉ ሰዎች የእግዚአብሄር ልጅ ሲሆኑ እንዴት እንደሚኖሩ ለማሳየት ነው፡፡ ኢየሱስ ወደ ምድር የመጣውና የተመላለሰው የእግዚአብሄር ልጅ ክብር ምን እንደሆነ ለሚመጡት ልጆች ለማሳየት ነው፡፡ ኢየሱስ በምድር ላይ እንደሰው የተመላለሰው ለተከታይ የእግዚአዘብሄር ልጆች የእግዚአብሄር ልጅነትን የክብር ደረጃ ሊያሳየን ነው፡፡
ኢየሱስ የመጀመሪያ ልጅ ነው፡፡ እኛ የእየሱስ ተከታዮች ሁለተኛ ሶስተኛ አራተኛ ሚሊዮነኛ . . . ልጆች ነን፡፡
ከኢየሱስ በፊት የእግዚአብሄር ልጅ በምድር ላይ ስላልነበረ የእግዚአብሄር ልጅነት ደረጃ ምን እንደሆነ አንረዳም ነበር፡፡ ከኢየሱስ በፊት የእግዚአብሄር ልጅነት ክብር ምን አይነት ክብር እንደሆነ አናውቅም ነበር፡፡ ኢየሱስን እስከምናየው ድረስ የእግዚአብሄር ልጅነት ማእረግ ደረጃውን አናውቅም ነበር፡፡ በኢየሱስ ካልሆነ በስተቀር የእግዚአብሄር ልጅነትን መብት የምናውቅበት ምንም መንገድ አልነበረም፡፡
ኢየሱስ ሲመጣ ግን የእግዚአብሄር ልጅነትን መብት አሳየን፡፡ ኢየሱስ በምድር ሲመለስ ልጅ በአባቱ ዘንድ ያለውን ማእረግ አሳየን፡፡ ስንፈጠር በእግዚአብሄር መልክና አምሳል እንደፈጠርን ሁሉ የተጠራነው የልጁን የኢየሱስን መልክ እንድንመስል ነው፡፡
ልጁ በብዙ ወንድሞች መካከል በኵር ይሆን ዘንድ፥ አስቀድሞ ያወቃቸው የልጁን መልክ እንዲመስሉ አስቀድሞ ደግሞ ወስኖአልና፤ አስቀድሞም የወሰናቸውን እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤ የጠራቸውንም እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውንም እነዚህን ደግሞ አከበራቸው። ሮሜ 8፡29-30
አባት ልጁን እንዴት እንደሚሰማው ያየነው በኢየሱስ ነው፡፡ አባት ልጁን እንዴት እንደሚወደው ያለየነው በኢየሱስ ነው፡፡
እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል። ዮሐንስ 17፡22-23
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የልጅነትክብር #ናሙና #መልክ #አምሳል #ልጅ #አባት #ክብር #ማእረግ #መብት #ስልጣን #ስፍራ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ቃል #ሞዴል #መምሰል #የእግዚአብሄርእቅድ #የእግዚአብሄርፈቃድ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment