Popular Posts

Saturday, November 25, 2017

ሕይወት የሚገኝበትን ትምህርት

ምግብ ለሰውነታችን እጅግ አስፈላጊ እንደሂነ ሁሉ የእግዚአብሄር ቃል ምግብ ለመንፈሳዊ ህይወታቸን አስፈላጊ ነው፡፡

በተፈጥሮ ለምግባችን እጅግ ልዩ ትኩረት እንደምንሰጥ ሁሉ ለመንፈሳዊ ምግባችን ልዩ ትኩረት መስጠት አለብን፡፡ በስጋዊ ምግብ ለጥቂት ደቂቃ መራብ እንደማንፈልግ ሁሉ የእግዚአብሄር ቃል ረሃንብ ሳይረካ እንዲቆት ማድረግ የለዐብንም፡፡ ሰው መንፈሱ የሚኖረው የሚመገበው የሚበረታው መንፈስ የሆነውን የእግዚአብሄርን ቃል በመመገብ ነው፡፡

ለሰውነታችን ሁለንተናዊ እድገት የምግብ ጥራት ወሳኝ እንደሆነ ሁሉ ለመንፈሳዊ ህይወታችን ጥራት የምንሰማው ቃል ጥራት ወሳኝ ነው፡፡ እንደ እግዚአብሄር ቃል የሆነ ትምህርት ህይወታቸንነ ያሳድገዋል መንፈሳ አቅም ይሰጠናል ከመንፈሳዊ በሽታ የምንካላከልበት አቅም ይሰጠናል፡፡  

የምንበላው መግብ ከበሽታ እንደሚከላከልልን ሁሉ የምንሰማው ቃል ከመንፈሳ በሽታ ይከላከልልናል፡፡

በሳይንስ አብዛኛው በሽታ ምግብን በማስተካከል ብቻ መከላከል ይቻላል፡፡ እንዲሁ የምንሰማው የእግዚአብሄቃል በስጋዊ ባህሪ ውስጥ ያለውን የህይወት በሽታ ይከላከልልናል፡

ስለዚህ ርኵሰትን ሁሉ የክፋትንም ትርፍ አስወግዳችሁ፥ ነፍሳችሁን ማዳን የሚችለውን በውስጣችሁም የተተከለውን ቃል በየዋህነት ተቀበሉ። ያዕቆብ 1፡21

እንዲሁ በተፈጥሮ የምንበላው ምግብ በአንዳድዳ ነገር ከተበከለ ጤናችንን እንደሚጎዳው ሁሉ ከእግዚአብሄር ቃል ውጭ የሆነ ትምህርት መንፈሳዊ ጤንናታችንን ይጎዳል እግዚአብሄር ካጠራን የህይወት አላማ ያሰናክላል፡፡ ስለዚህ ነው ሃዋሪያው ጳውሎስ ለጢሞቲዮስ ለትምህርቱ እንዲጠነቅቅ የሚያዘው፡፡

ለራስህና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ፥ በእነዚህም ጽና፤ ይህን ብታደርግ፥ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህና። 1ኛ ጢሞቴዎስ 4:16
ጤናማ ቃል ጤናማ ህይወት ይሰጣል፡፡ ጤናማ ያልሆነ ቃል የመንፈሳዊ ህይወትን ጤንነት ያውካል፡፡ ጤናማ ትምህርት ህይወትን ያለመልማል፡፡ ጤናማ ያልሆነ ትምህርት ህይወትን ያቀጭጫል፡፡ ጤናማ ትምህርት ለአግዚአብሄር ይበልጥ እንድንሰጥ ያበረታል፡፡ ጤናማ ያልሆነ ትምህርት በእግዚአብሄር ተስፋ እንድንቆርጥ ያደርጋል፡፡ ጤናማ ትምህርት በትክክለኛው ነገር ላይ እንድናተኩር ያደርጋል፡፡ ጤናማ ያልሆነ ትምህርት በተሳሳተ ነገር ላይ አተኩረን ፍሬ ቢስ እንድንሆን ያደርጋል፡፡  
ዳሩ ግን ባለ ጠጎች ሊሆኑ የሚፈልጉ በጥፋትና በመፍረስ ሰዎችን በሚያሰጥምና በሚያሰንፍ በሚጎዳም በብዙ ምኞትና በፈተና በወጥመድም ይወድቃሉ። ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር ነውና፥ አንዳንዶች ይህን ሲመኙ፥ ከሃይማኖት ተሳስተው በብዙ ሥቃይ ራሳቸውን ወጉ። 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡10
በክርስቶስ ኢየሱስ ባለ እምነትና ፍቅር አድርገህ፥ ከእኔ የሰማኸውን ጤናማ ቃል ምሳሌ ያዝ፤ 2 ጢሞቴዎስ 113
የሚቃወም ሰው ስለ እኛ የሚናገረውን መጥፎ ነገር ሲያጣ እንዲያፍር፥ በነገር ሁሉ መልካምን በማድረግህ ምሳሌ የሚሆን ራስህን አሳይ፤ በትምህርትህም ደኅንነትን፥ ጭምትነትን፥ ጤናማና የማይነቀፍ ንግግርን ግለጥ። ቲቶ 27-8
ጤናማ ትምህርት አልጋ በአልጋ የሆነ ትምህርት ሳይሆን ለእግዚአብሄርና ለእግዚአብሄርር ብቻ እንድንኖር የሚያስጨክን አለምን እንድንክድ በምድር ላይ እንደ እንግዶችና መጻተኞች እንድንኖር የሚያበረታ ትምህርት ነው፡፡
ስለዚህ ወንድሞችን ብታሳስብ፥ በእምነትና በተከተልኸው በመልካም ትምህርት ቃል የምትመገብ የኢየሱስ ክርስቶስ መልካም አገልጋይ ትሆናለህ። 1 ጢሞቴዎስ 4፡6
ሕይወት የሚገኝበትን ትምህርት የማይታገሡበት ዘመን ይመጣልና፤ ነገር ግን ጆሮቻቸውን የሚያሳክክ ስለ ሆነ፥ እንደ ገዛ ምኞታቸው ለራሳቸው አስተማሪዎችን ያከማቻሉ። 2 ጢሞቴዎስ 4፡3
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እግዚአብሄር #አስተማሪ #ቃልኪዳን #መልካምትምህርት #ጤንነት #ንፁህ #አትለፍ #ትምህርት # #ፍሬ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አትጨነቁ  #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment