Popular Posts

Wednesday, November 29, 2017

የፍሬያማነት ብቸኛው መንገድ

በእኔ ኑሩ፤ እኔም በእናንተ፤ ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ከአልኖረ ብቻውን ሊያፈራ እንደማይችል እናንተም እንዲሁ በእኔ ካልኖራችሁ ፍሬ ማፍራት አትችሉም። ዮሐንስ 15፡4
ፍሬያማነት ሁሉም ሊያገኘው የሚፈልገው እጅግ መልካም ነገር ነው፡፡ ፍሬያማነት የስኬት ፣ የብልፅግናና የሙላት ጣራ ነው፡፡ ፍሬያማ እንደ መሆናችን የሚያስደስት ነገር በምድር ላይ የለም፡፡
ፍሬማነት ሊታወቅ የማይችል ፣ ሊመዘን የማይችል ፣ ሊረዱት የማይችል ረቂቅ ነገር አይደለም፡፡
ፍሬያማነት በአጋጣሚ የምንመታው እድል አይደለም፡፡ የክርስትና ፍሬማነት እስከምናገኘው ድረስ እርግጠኛ የማንሆንበት መጀመሪያውና መጨረሻው የማይታወቅ በእድል ብቻ የሚገኝ ነገር አይደለም፡  
በክርስትና ፍሬያማነት የሚለካበት ከመረዳት በላይ የሆነ ውስብስብ መንገድ የለም፡፡ በክርስትና ፍሬያማ መሆናችን ወይም አለመሆናችን የሚለካው በአንድ መመዘኛ ብቻ ነው፡፡
በእኔ ኑሩ፤ እኔም በእናንተ፤ ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ከአልኖረ ብቻውን ሊያፈራ እንደማይችል እናንተም እንዲሁ በእኔ ካልኖራችሁ ፍሬ ማፍራት አትችሉም። ዮሐንስ 15፡4
የክርስትና ፍሬያማነት ብዙ አይነት ትርጉም የለውም፡፡ የክርስትናን ፍሬያማነት ሊገልፅልን የሚችለው የእግዚአብሄር ቃል ብቻ ነው፡፡ የክርስትና ፍሬያማነት የሚወስነው እግዚአብሄር ራሱ ነው፡፡ ስለ ፍሬያማነተ ክርክር ቢነሳ ሊወስን የሚችል የመጨረሻው አካል እግዚአብሄር ነው፡፡ እግዚአብሄር ፍሬያማነት ይህ ነው ካለ ማንም አይከራከርም የክርክር ፍፃሜ ይሆናል፡፡
ፍሬያማነት በሰዎች የተለያዩ መመዘኛዎች አይመዘንም ፡፡ ፍሬያማነት በዘመኑ ሁኔታ አይለዋወጥም፡፡ የክርስትና ፍሬያማነት እንደሰው አይለያይም፡፡ የክርስትና ፍሬያማነት አንድና እንድ ብቻ ነው፡፡
በእኔ ኑሩ፤ እኔም በእናንተ፤ ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ከአልኖረ ብቻውን ሊያፈራ እንደማይችል እናንተም እንዲሁ በእኔ ካልኖራችሁ ፍሬ ማፍራት አትችሉም። ዮሐንስ 15፡4
በክርስትና ፍሬያማ ለመሆነ መንገዱ አንድና አንድ ብቻ ነው፡፡ በክርስትና ፍሬያማ ለመሆን 99 መንገዶች የሉትም፡፡ በክርስትና ፍሬያማ ለመሆን ብዙ አማራጮች የሉትም፡፡ በክርስትያ ፍሬያማ የመሆን መንገዱን እኛ እንወስነውም፡፡  
በፍሬያማነት ለመኖር በኢየሱስ መኖር በቂ ነው፡፡ ፍሬያማነት የሚመዘነው ሃብት በማግኘታችን ፣ ዝነኛ በመሆናችን ወይም ደግሞ ታላቅ ነገር በመስራታችን አይደለም፡፡ ፍሬያማነት የሚመዘነው በኢየሱስ መኖራችን ብቻ ነው፡፡ በኢየሱስ የሚኖር ሰው ፍሬያማ ነው፡፡ በኢየሱስ የማይኖር ሰው ፍሬያማ አይደለም፡፡ በኢየሱስ መኖራችን ብቻ ፍሬያማ ያደርገናል፡፡ በኢየሱስ አለመኖራችን ብቻ ፍሬቢስ ያደርገናል፡፡ የሰው ፍሬያማነት የሚለካው በኢየሱስ በመኖሩ መጠን ነው፡፡ 50% በኢየሱስ የሚኖር ሰው 50% ፍሬያማ ይሆናል ፣ 10% በኢየሱስ የሚኖር 10% ፍሬያማ ይሆናል ፣ 100% በኢየሱስ የሚኖር 100% ፍሬያማ ይሆናል፡፡
በኢየሱስ በመኖራችን ብቻ በፍሬያማነት እየኖርን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በኢየሱስ መኖራችን ብቻውን ሌላ ሌላ ነገር ሳይጨምር በእውነት ፍሬያማ ያደርገናል፡፡  
የክርስትያን ፍሬያማነት ለመለካት ውስብስብ መመዘኛዎች የሉትም፡፡  የክርስትናን ፍሬያማነት ለመመዘን ያለው አንድ መስፈርት በኢየሱስ መኖር ነው፡፡
እንደ እግዚአብሄር መዝገበ ቃላት የክርስትና ፍሬያማነት ትርጉም በኢየሱስ መኖር ነው፡፡
የፍሬያማነት አንድና አንድ መመዘኛ በኢየሱስ መኖር ብቻ ነው፡፡ ፍሬያማነት ብዙ አማራጭ መንገዶች የሉትም፡፡ በኢየሱስ መኖር አንዱና ብቸኛ የፍሬያማነት መንገድ ነው፡፡
በእኔ ኑሩ፤ እኔም በእናንተ፤ ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ከአልኖረ ብቻውን ሊያፈራ እንደማይችል እናንተም እንዲሁ በእኔ ካልኖራችሁ ፍሬ ማፍራት አትችሉም። ዮሐንስ 15፡4
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ሬያማነት #ፍሬ #ማፍራት #ስኬት #በእኔኑሩ #ቃል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መመዘኛ #መስፈርት #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment