Popular Posts

Saturday, June 3, 2017

ልባችሁ አይታወክ አይፍራም

ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም። ዮሐንስ 14፡27
በልባችን ሰላም ካለን ሁሉ ነገር መልካም ነው፡፡ ውጭው ተረብሾ የውስጥ ሰላም ካለን  ነገር ሁሉ ትክክል ነው፡፡ በአእምሮዋችን ግራ መጋባት ኖሮ በልባችን ሰላም ካለን ሁሉ ሰላም ነው ማለት ነው፡፡ ልባችሁ ብቻ አይታወክ እንጂ ሌው ችግር የለም ብሎናል፡፡
ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ። ዮሐንስ 14፡1
ከውጭ ያለው ነገር እንደማይታወክ መተማመኛ የለንም፡፡ ልባችንን በሰላም እንደሚጠብቀው ግን ቃል ግብቶልናል፡፡   
ምንም ምንም መከተል ባትችሉ የልባቸሁን ሰላመ ተከተሉ፡፡ በውጭው ምንም ነገር ባትተማመኑ በልባችሁ ሰላም ተማመኑ፡፡ ምንም የውጭ ነገር እንዲመራችሁ ባትፈቅዱ የልባችሁ ሰላመ ይምራችሁ፡፡  
በአንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ፤ የምታመሰግኑም ሁኑ። ቆላስይስ 3፡15
እንዲያውም በአለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ብሎዋል፡፡ ነገር ግን አይዞዋችእሁ እኔ አለምን አሸንፌዋለሁ፡፡ እናንትም እያሸነፋችሁት ነው፡፡ ስለዚህ ሰላማችሁን አትጡ፡፡ ሰላማችሁ አይወሰድ፡፡ ሰላም ነው እያለን ነው፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መታዘዝ #ተስማማ #ሰላም #ልብ #አይታወክ #አይፍራ #ስኬት ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ፀጋ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment