Popular Posts

Tuesday, June 27, 2017

የሰራዊት ጌታ እንደዚህ ይላል

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል፡፡ ትታመኑብኝ አልነበረምን? ሁሉን ጥላችሁ ተከትላችሁኝ አልነበረምን? ከእኔ ውጭ መተማመኛ ሳትፈልጉ አላገለገላችሁኝምን?
ታዲያ እኔን ታምናችሁ በወጣችሁ ጊዜ ምን ጎደለባችሁ? ታዲያ በላክኋችሁ ጊዜ ምን አጎደልኩባችሁ ይላል እግዚአብሄር? ያላደረግኩላችሁ ነገር ነበርን ይላል የሰራት ጌታ እግዚአብሄር?
ታዲያ አሁን ከእኔ ውጭ ደህንነትን ለምን ፈለጋችሁ? ታዲያ በቁሳቁስና በገንዘብ ደህንነትን ለምን ፈለጋችሁ ይላል እግዚአብሄር? ቦዶ እጃችሁን እንዳልተከተላችሁኝ ያላችሁ ለምን አልበቃ አላችሁ ይላል እግዚአብሄር? እኔ አልለወጥም ይላል እግዚአብሄር፡፡
ስትደገፉብኝ ፣ ፊቴን ስትፈልጉ ፣ ጌታ ጌታ ስትሉኝ ያረካኛል ይላል እግዚአብሄር፡፡ በእኔ ተደገፉብኝ ፣ እኔ ብቻ ደህንነታችሁ ልሁን ይላል እግዚአብሄር፡፡ ያላችሁ ምንም ነገራችሁ ደህንነት አይሁናችሁ ይላል እግዚአብሄር፡፡  
አሁንም ተመለሱ ይላል እግዚአብሄር፡፡ ቁሳቁስን ገንዘብን ከመፈለግ እኔን ፈልጉ ይላል እግዚአብሄር፡፡ በእኔ ውስጥ የህይወታችሁ ጥያቄ ሁሉ መልስ አለ ይላል እግዚአብሄር፡፡ የምትፈልጉት ሁሉ እኔ ውስጥ አለ ይላል እግዚአብሄር፡፡
እኔ አልለወጥም፡፡ እስከ ሽምግልና የምሸከምህ እኔ ነኝ ይላል እግዚአብሄር፡፡
ባላችሁ ነገር ሳይሆን በእኔ ላይ ስትደገፉ ደስ ይለኛል ይላል እግዚአብሄር፡፡ በእኔ ላይ ስትደገፉ ብቻ ያረካኛል ይላል እግዚአብሄር፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #መናገር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ቃል #ማሰላሰል #ማድረግ #ሁሉይቻላል #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment