Popular Posts

Tuesday, April 18, 2017

የእግዚአብሄር መንግስት እንጂ ባለጠግነት ጉልበትህና ድካምህ አይገባውም

ለእግዚአብሄር ልጅ የገባውና የሚመጥነው ለእግዚአብሄር መንግስት መስራት ነው፡፡ የባለጠግነት ሩጫ ለእግዚአብሄር ልጅ አይገባም፡፡ ባለጠጋ ለመሆን መድከም ለእግዚአብሄር ልጅ የማይመጥነው ተራ ነገር ነው፡፡ ባለጠግነት ጉልበታችንና ድካማችን የማይገባው ተራ ነገር ነው፡፡
ባለጠጋ ለመሆን አትድከም፤ የገዛ ራስህን ማስተዋል ተው። በእርሱ ላይ ዓይንህን ብታዘወትርበት ይጠፋል፤ ባለጠግነት ወደ ሰማይ እንደሚበርር እንደ ንስር ለራሱ ክንፍ ያበጃልና። ምሳሌ 23፡3-5
 ኢየሱስ በምድር በተመላለሰበት ጊዜ  ለመብል ብለው የተከተሉትን ሰዎች ለእግዚአብሄር እንዲሰሩ አንጂ ለሚጠፋ መብል እንዳይሰሩ ያስተምራቸዋል፡፡
ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፤ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፤ እርሱን እግዚአብሔር አብ አትሞታልና። ዮሃንስ 6፡27
እጅግ ሃያል የሆነው የእግዚአብሄር ቃል በህይወታችን እንዳይሰራና ፍሬያማ እንዳንሆን የሚያደርገው የባለጠግነት ማታለል ነው፡፡
የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት ማታለል የሌላውም ነገር ምኞት ገብተው ቃሉን ያንቃሉ፥ የማያፈራም ይሆናል።ሉቃስ 4፡19
ስለዚህ ነው ኢየሱስ ለሁለት ጌቶች መገዛት አትችሉም ያለው፡፡ ለባለጠግነት መድከም ጌታን የማያውቁ የመንግስቱ አላማ የሌላቸው በኑሮ ከመካት የተሻለ አላማ በህይወታቸው የሌላቸው የተራ ሰዎች አካሄድ ነው፡፡
ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። ማቴዎስ 6፡32-33
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ጭንቀት #የባለጠግነትማታለል #የኑሮሃሳብ #የእለትእንጀራ #የባለግነትምቾት #ዘር #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment