Popular Posts

Saturday, August 21, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 6

 


የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 6

እግዚአብሄር ሰዎችን መፈወስ ይወዳል፡፡ 

ኢየሱስ በምድር ላይ በሚመላለስበት ጊዜ አንድ ለምፃም ወደ እርሱ ቀርቦ ብትወድስ ልታነጻኝ ትችላለህ አለው፡፡ ለምፃሙ ስለኢየሱስ የመፈወስ ችሎታ አልተጠራጠረም፡፡ 

ብዙ ሰው ስለእግዚአብሄር የመፈወስ ችሎታ አይጠራጠርም፡፡ 

አንዳንድ ሰው ግን ፈውስ የእግዚአብሄር ፈቃድ እንደሆነ እርግጠኛ አይደለም፡፡ 

እነሆም፥ ለምጻም ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ ብትወድስ ልታነጻኝ ትችላለህ እያለ ሰገደለት። እጁንም ዘርግቶ ዳሰሰውና፦ እወዳለሁ፥ ንጻ አለው። ወዲያውም ለምጹ ነጻ። ማቴዎስ 8፡2-3

የኢየሱስ መልስ ግን እግዚአብሄር ሰዎችን መፈወስ እንደሚችል ብቻ ሳይሆን እግዚአብሄር ሰዎችን መፈወስ እንደሚፈልግና እንደሚወድ ያሳያል፡፡ 

አንደኛው የእግዚአብሄር ስም ፈዋሽ አምላክ የሚል ነው፡፡ እግዚአብሄር በመፈወስ ይታወቃል፡፡ እግዚአብሄር ሰዎችን ሙሉ በማድረግ 

ኢየሱስንም በታላቅ ቅናት እና ትጋት በያሉበት ሁሉ በመሄድ ሰዎችን ይፈውስ ነበር፡፡ 

እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤ ሐዋሪያት 10፡38

ይህ የኢየሱስ አገልግሎት የእግዚአብሄርን የመፈወስ ታላቅ ቅናት ያሳያል፡፡ 

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa 

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment