Popular Posts

Sunday, August 22, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 7

 

ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ስለነፍሳችን ዋጋ ሊከፍል ብቻ አይደለም፡፡ ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ስለነፍሳችን ሃጢያት ዋጋ ሊከፍልና እንዲሁም ደግሞ በሃጢያት ምክኒያት ስለመጣብን በሽታ ዋጋን ሊከፍል ጭምር ነው፡፡ ኢየሱስ ስለ ሃጢያታችን ሞተ ስለህመማችን ተገረፈ፡፡

በመሸም ጊዜ አጋንንት ያደረባቸውን ብዙዎችን ወደ እርሱ አመጡ፤ በነቢዩ በኢሳይያስ፦ እርሱ ድካማችንን ተቀበለ ደዌያችንንም ተሸከመ የተባለው ይፈጸም ዘንድ፥ መናፍስትን በቃሉ አወጣ፥ የታመሙትንም ሁሉ ፈወሰ። ማቴዎስ 8፡16-17

ሰው ነፍሱ ሁሉ ድኖ ነገር ግን ስጋው ካልተፈወሰ በምድር ላይ እግዚአብሄርን እንደሚገባው ሊያገለግል አይችልም፡፡ የሰው ነፍስ ከእስራት ድኖ ስጋው ግን ከህማምና ከበሽታ ነፃ ካልሆነ እግዚአብሄርን በምድር ላይ እንደሚገባው ለረጅም ጊዜ ሊያገለግል አይችልም፡፡  

ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። 1ኛ ጴጥሮስ 2፡24

ኢየሱስ በምድር ላይ በተመላለሰ ጊዜ ሁሉ ስለነፍስ የሃጢያት እስራት መድሃኒት የሆነውን የእግዚአብሄርን ቃል ሰብኮዋል፡፡ እንዲሁም ስለስጋቸው መፈወስ በትጋት የፈውስ አገልግሎትን ሲያደርግ እንመለከተዋለን፡፡

እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤ ሐዋሪያት 10፡38 

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

 

No comments:

Post a Comment