Popular Posts

Friday, January 20, 2017

የሰይጣን ብቸኛው መሳሪያ

የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ። ኤፌሶን 6፡11
የጠላት የዲያብሎስ አላማ መስረቅ ማረድና ማጥፋት ነው፡፡ ዲያቢሎስ የተሸነፈ ጠላት ነው፡፡ ኢየሱስ ሰይጣንን በመስቀል ላይ ድል ነስቷል፡፡
አለቅነትንና ሥልጣናትን ገፎ፥ ድል በመንሣት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሳያቸው። ቆላስይስ 2፡15
ሰይጣን የተሸነፈ ጠላት ነው፡፡ ሰይጣን ማንንም በግድ ጎትቶ ሃጢያት ሊያሰራ አይችልም፡፡ ሰይጣን እንደታሰረ ውሻ ነው፡፡ የታሰረ ውሻ እንደሚጮህና እንደሚረብሽ ሁሉ ሰይጣንም መሳሪያው ጩኸት ፣ ማስፈራራትና ማታለል ብቻ ነው፡፡ ሰይጣን የጥርጥርን ሃሳብ ወደ አእምሮዋችን ልኮ ከተቀበልነው ከእምነት መንገድ እንስታለን፡፡
ሰይጣን ሃሳብን ወደ አእምሮው ልኮ በሰይጣን ሽንገላ የተሸነፈ ሰው የሰይጣንን ማስፈራሪያ ፈርቶ ከመንገዱ ይመለሳል፡፡ በሰይጣን ሽንገላ የተታለለ ሰው በኑሮ ፍርሃት እግዚአብሄርን ከማገልገል ይመለሳል፡፡
የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት ማታለል የሌላውም ነገር ምኞት ገብተው ቃሉን ያንቃሉ፥ የማያፈራም ይሆናል። ማርቆስ 4፡19
በሰይጣን የሃጢያት ሽንገላ የተታለለ ሰው ለእግዚአብሄር በቅድስና መኖር አይቻልም ብሎ ተስፋ ይቆርጣል፡፡ በሰይጣን ሽንገላ የተሸነፈ ሰው አለምን ማሸነፍ አይቻልም ብሎ ለአለም አሰራር እጅ ይሰጣል፡፡
ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም። 1ኛ ዮሐንስ 2፡15-16
ሰይጣን ስልጣኑ ስለተገፈፈ ብቸኛው መሳሪያው ማታለል ነው፡፡ ሰይጣን ካታለለን ክፋት ያሰራናል፡፡ ሽንገላውን ከተቃወምን እግዘኢአብሄርን አገልግለን እናልፋለን፡፡
ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ ከማታለሉ እንድንጠበቅ የሚመክረን፡፡ ከማታለሉ የምንጠበቀው የእግዚአብሄርን ቃል ስንረዳ ብቻ ነው፡፡ ከሰይጣን ማታለል የምንጠበቀው በእግዚአብሄር ጥበብ ብቻ ነው፡፡
የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ። ኤፌሶን 6፡11
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ሰይጣን #ዲያብሎስን #ሽንገላ #ሃሳብ #አእምሮ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ብፅእና  #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment