Popular Posts

Saturday, January 21, 2017

ምን ብዬ ልጩኽ?

ጩኽ የሚል ሰው ቃል፤ ምን ብዬ ልጩኽ? አልሁ። ሥጋ ለባሽ ሁሉ ሣር ነው፥ ክብሩም ሁሉ እንደ ምድረ በዳ አበባ ነው። የእግዚአብሔር እስትንፋስ ይነፍስበታልና ሣሩ ይደርቃል አበባውም ይረግፋል፤ በእውነት ሕዝቡ ሣር ነው። ሣሩ ይደርቃል አበባውም ይረግፋል፥ የአምላካችን ቃል ግን ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች። ኢሳይያስ 40፡6-8
የሰው ህይወት በምድር ላይ አጭር ነው፡፡ ሰው ሃላፊ ነው፡፡ የሰው ህይወቱ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ነው፡፡
ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና። ያዕቆብ 4፡14
ሰው ሰማይና ምድርን ከፈጠረው ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላለም መኖር የሚችለው የእግዚአብሄርን የመዳኛ መንገድ ሲቀበል ብቻ ነው፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላለም መኖር የሚችለው የማይጠፋውን የእግዚአብሄርን ቃል ሲቀበል ብቻ ነው፡፡ ሰው የዘላለም ህይወት የሚኖረው እግዚአብሄር ስለመዳኑ ያዘጋጀውን የኢየሱስን የመስቀል ስራ ለእኔ ነው የሞተውና የተነሳው ብሎ ብቻ ነው፡፡
በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። ዮሃንስ 3፡16
ሰው ዘላለማዊ ህይወትን የሚያገኘው ከእግዚአብሄር ቃል ዳግመኛ ሲወለድ ብቻ ነው፡፡
ሰማይና ምድር ያልፋሉ ከማይጠፋው ለዘላለም ከሚኖረው ከእግዚአብሄር ቃል የተወለደ ሰው ግን አያልፍም፡፡
ዳግመኛ የተወለዳችሁት ከሚጠፋ ዘር አይደለም፥ በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ ዘር ነው እንጂ። ሥጋ ሁሉ እንደ ሣር ክብሩም ሁሉ እንደ ሣር አበባ ነውና፤ ሣሩ ይጠወልጋል አበባውም ይረግፋል፤ የጌታ ቃል ግን ለዘላለም ይኖራል። በወንጌልም የተሰበከላችሁ ቃል ይህ ነው።  1ኛ ጴጥሮስ 1፡23-25
ኢየሱስ ስለሃጢያቱ እንደሞተለትና ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ የሚያምን ሰው ይድናል፡፡
ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። ሮሜ 10፡9-10
ሰማይና ምድር ያልፋሉ፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ግን አያልፍም፡፡
ሰማይና ምድር ያልፋሉ፥ ቃሌ ግን አያልፍም። ማቴዎስ 24፡35
የሚታየው ሁሉ የጊዜው ነው፡፡ የማይታየው ሁሉ ዘላለማዊ ነው፡፡
የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው። 2ኛ ቆሮንቶስ 4፡18
ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል። 1ኛ ዮሃንስ 2፡17
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የጌታቃል #ዘላለም #የዘላለምህይወት #የእግዚአብሄርፈቃድ #የጊዜው #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ብፅእና  #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment