Popular Posts

Saturday, December 31, 2016

አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን

እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። ማቴዎስ 6፡31-33
በሃጢያት ምክኒያት የሰው ቅድሚያ አሰጣጥ ተዛብቷል፡፡ ይህ ቅደም ተከተል ካልገባው የሰው ህይወት ከንቱ ሩጫ ነው፡፡ ሰው ይህን ቅደም ተከተል ካላስተካከለ በህይወቱ የሚስተካከል ምንም ነገር አይኖርም፡፡  
ኢየሱስም አለ ስለምትበሉትና ስለምትጠጡት አትጨነቁ፡፡ መብላትና መልበስ የህይወት አላማችሁ አይሁን፡፡ መጠጣትና መልበስን እንደ ራእይ አትያዙት፡፡ መብላትና መጠጣትን መከተል አይመጥናችሁም፡፡ መብላትና መልበስን መፈለግ የእግዚአብሄር ቤተሰብ አባልነት ክብራችሁ አይመጥነውም፡፡ ከመብላትና መጠጣት ያለፈ ክብር ያላችሁ ሰዎች ናችሁ፡፡ ከመጠጣትና ከመልበስ እጅግ የላቅ ጥሪ አላችሁ፡፡ የሚበላና የሚጠጣ ከመፈለግ የተሻለ ክብር አላችሁ፡፡
መብላትና መጠጣትን መፈለግ ክብር አይደለም፡፡ የሚበላውና የሚለበሰውን መፈለግ ትልቅ ነገር አይደለም፡፡ መብላትና መልበስን ማንም ሰው ፣ ማንም መንገደኛ ፣ ማንም ተራ ሰው ይፈልገዋል፡፡
ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ማቴዎስ 6፡32
እግዚአብሄር አያስፈልጋችሁም እያለ አይደለም፡፡ ይህ ለኑሮ እንደሚያስፈልግ አባታችሁ ያውቃል፡፡ እግዚአብሄርን አታስረዱትም፡፡ ስለ ባተሌነታችሁ ለእግዚአብሄር የሚበላና የሚጠጣ ለመፈለግ ነው ብላችሁ ለእግዚአብሄር ምክኒያትን አትሰጡትም፡፡
ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና።
እግዚአብሄር እያለ ያለው የሚበላ የሚጠጣ የሚለበስ መፈለግ ድርሻችሁ አይደለም፡፡ አስቀድማችሁ ድርሻችሁን አድርጉ፡፡ አስቀድማችሁ የሚመጥናችሁን አድርጉ፡፡ አስቀድማችሁ የተጠራችሁትን አድርጉ፡፡ አስቀድማችሁ የቤተሰቡን ክብር ጠብቁ፡፡ አስቀድማችሁ መንግስቱን ተንከባከቡ፡፡ አስቀድማችሁ መንግስቱን ፈልጉ፡፡
ይህ ሁሉ ይጨመርላችኋል፡፡ ይህ ሁሉ ተጨማሪ ነው፡፡ ይህ ሁሉ ምርቃት ነው፡፡ ይህን ሁሉ እስከማትፈልጉ ድረስ እግዚአብሄር የድርሻውን ያደርጋል፡፡ እግዚአብሄር ያቀርባል፡፡ ይጨመርላችኋል፡፡
ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። ማቴዎስ 6፡33
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#አትጨነቁ #ቅድሚያ #ምንእንበላለን #ምንእንጠጣለን #ምንእንለብሳለን #አስቀድማችሁ #ፅድቁን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ምህረት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment