Popular Posts

Thursday, April 25, 2019

የተከፈለለት ባለእዳ



እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁ ኑና ግዙ ብሉም፤ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅና ወተት ግዙ። ገንዘብን እንጀራ ላይደለ፥ የድካማችሁንም ዋጋ ለማያጠግብ ነገር ለምን ትመዝናላችሁ? አድምጡኝ፥ በረከትንም ብሉ፥ ሰውነታችሁም በጮማ ደስ ይበለው። ትንቢተ ኢሳይያስ 55፡1-2
የሃጢያት ደሞዝ ሞት ነው፡፡ በሃጢያታችን ባለ እዳ ነበርን፡፡ ሃጢያት ከእዳዎች ሁሉ የከፋ እዳ ነው፡፡ ሃጢያት ሸክም ነው፡፡ ሃጢያት እስራት ነው፡፡ በሃጢያታችን ለዘለዓለም ከእግዚአብሄር መለያየት ነበረብን፡፡
ስለሃጢያትን በራሳችን ዋጋ መክፈል አንችልም፡፡ የትኛውም መልካም ስራችን ስለሃጢያታችን ክፍያ በቂ አይደለም፡፡
እኛ በሃጢያታችን ምክኒያት ለዘላለም ከእግዚአብሄር እንዳንለያይ ሃጢያት የሌለበት ኢየሱስ ስለሃጢያታችን እኛን ተክቶ በመስቀል ላይ ሊሞት ወደምድር መጣ፡፡ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ስለሃጢያታችን ሙሉ ዋጋን ከፍሏል፡፡
ኢየሱስ በመስቀል ላይ ስለሃጢያቱ ሙሉ ክፍያን እንደከፈለ ያላመነ ሰው ባለእዳ ሆኖ ይኖራል፡፡ ኢየሱስ በመስቀል ላይ የከፈለለትን ለእኔ ነው ብሎ የማይቀበል ሰው የእግዚአብሄር ቁጣ በእርሱ ላይ ስለሚኖር በምድር ባለእዳ ሆኖ በጉስቁልና ይኖራል፡፡  
በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም። የዮሐንስ ወንጌል 3፡36
ኢየሱስ እኛን ሃጢያተኞችን ወክሎ በእኛ ፋንታ በመስቀል ላይ እንደሞተ የሃጢያታችንን እዳ ሁሉ በመስቀል ላይ እንደከፈለ የማያምን  ሰው ለዘላለም ከእግዚአብሄር በመለያየት የሃጢያቱን እዳ በራሱ ይከፍለዋል፡፡
በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤ ወደ ገላትያ ሰዎች 3፡13
ኢየሱስ በመስቀል ላየ ዋጋ መክፈሉ የሚጠቅምህና ከዘላም ጥፋተ የሚያድንንህ በእምነት ስትቀበልው ብቻ ነው፡፡ ኢየሱስ አንተን ተክቶ  በመስቀል ላይ የከፈለውን ዋጋ በእምነት ካለተቀበልክ እና ከሃጢያት እዳ ካልዳንክ እስከ ሃጢያትህ ትኖታለህ ትሞታለህ፡፡  
ይህንን ፀሎት ከልብህ በመፀለይ የእግዚአብሄር ልጅ አድርጎ እግዚአብሄር እንዲቀበልህ ማድረግ ትችላለህ፡፡
እግዚአብሄር ሆይ ሃጢያተኛ ነኝ፡፡ የሃጢያት ደሞዝ ደግሞ ለዘላለም ከአንተ መለየት ነው፡፡ እግዚአብሄር ከሃጢያት ለመዳኛ ያዘጋጀኸውን የሃጢያት መስዋእት ኢየሱስን እቀበላለሁ፡፡ እየሱስ ስለሃጢያቴ በእኔ ምትክ በመስቀል ላይ እንደተሰቀለና እንደሞተ ከሞትም እንደተነሳ አምናለሁ፡፡ ኢየሱስን በህይወቴ ላይ ጌታ አድርጌ እሾመዋለሁ፡፡ ኢየሱስን በህይወቴ ዘመን ሁሉ እከተለዋለሁ፡፡ እግዚአብሄር ሆይ ልጅህ አድርገህ ስለተቀበልከኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ የዘላለም ህይወት ስለሰጠኸኝ አመሰግናለሁ፡፡ በኢየሱስ ስም፡፡ አሜን፡፡
Abiy Wakuma Dinsa አቢይ ዋቁማ ዲንሳ
#አዲስፍጥረት #አዲስ #መዋጀት  #መዳን #ኢየሱስ #ጌታ #እግዚአብሔር #ንስሃ #አቁማዳ #መታዘዝ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ኦርቶዶክስ #ተዋህዶ #ጌታ #ማሪያም #መላእክት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ሰላም ትግስት #ልጅ

No comments:

Post a Comment