Popular Posts

Friday, April 5, 2019

ስፍራህን አትልቀቅ


ትዕግሥት ታላቁን ኃጢአት ጸጥ ያደርጋልና የገዢ ቍጣ የተነሣብህ እንደ ሆነ ስፍራህን አትልቀቅ። መጽሐፈ መክብብ 10፡4
እግዚአብሄር ሁልጊዜ ሊመራን ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር የመራህን ነገር እስከመጨረሻው ድረስ ማድረግ በጣም ወሳኝና ሁልጊዜ ፍሬያማ የሚያደርገን ነገር ነው፡፡
ሁኔታዎች ቢለዋወጡም እግዚአብሄር በፊት ከመራን ነገር ፈቀቅ ማለት የለብንም፡፡ እግዚአብሄር የተለየ ነገር ሲናገረን ብቻ መንገዳችንን መለወጥ ያለብን፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር እንድንለውጥ ሳይናገርህ መጨረሻ ላይ የመራንን ምሪት መከተል ትተን ሌላ ነገር ማድረግ ከአላማችን የሚያስተጓጉለን ነገር ነው፡፡
እግዚአብሄር እንድትለውጥ እስካልመራህ ድረስ እግዚአብሄር መጨረሻ ላይ መርቶህ ስታደርገው የነበረውን ነገር እንደማድረግ አስተማማም ምሪት የለም፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መንፈስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment