Popular Posts

Monday, April 8, 2019

ከእረፍት የሚጀምር ስራ


ክርስትና የእግዚአሄርን ሃሳብ በምድር ላይ ማስፈፀም ነው፡፡ ነገር ግን ክርስትና ከስራ አይጀምርም ፡፡ ክርስትና የጥረትና የግረት ጉዳይ ሳይሆን የእረፍት ጉዳይ ነው፡፡ ክርስትና የሚጀምርው ከእረፍት ነው፡፡ የክርስትና ሃይል የሚመነጨው ከእረፍታችን ነው፡፡ ክርስትና የሚቀጥለውም በእረፍት ነው፡፡ ክርስትና የሚጨርሰውም በእረፍት ነው፡፡
እውነት ነው ክርስትና መመላለስ ነው፡፡ ክርስትና መኖር ቃሉን በተግባር መፈፀም ነው፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ በፍቅር እንድንኖር ያዘናል፡፡ ነገር ግን የክርስትና ህይወት የሚጀምረው በፍቅር ከመኖር ሳይሆን የእግዚአብሄርን ፍቅር ከመረዳትና ከመቀበል ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ፍቅር የተረዳና በእግዚአብሄር ፍቅር የረካ ሰው ብቻ ነው ሌላውን ለመውደድ ሃይል የሚያገኘው፡፡ የእግዚአብሄርን ፍቅር የተካፈለ ሰው ብቻ ነው ፍቅርን ለሌሎች በእረፍት ሊያካፍል የሚችለው፡፡
ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5፡2
የእግዚአብሄርን ብርሃን ያላየና ያልተረዳ ሰው በብርሃን የሊመላለስ አይችልም፡፡ በብርሃን ሊመላለስ የሚችለው የእግዚአብሄርን ብርሃን ያየና የተረዳ ሰው ብቻ ነው፡፡
ነገር ግን እርሱ በብርሃን እንዳለ በብርሃን ብንመላለስ ለእያንዳንዳችን ኅብረት አለን፥ የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1፡7
ሰው የስጋን ምኞት የማይፈጽመው በነፃ የተሰጠውን ወደ እውነት ሁሉ የሚመራውን የእግዚአብሄርን መንፈስ መከተል ሲያውቅ ብቻ ነው፡፡
ነገር ግን እላለሁ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ። ወደ ገላትያ ሰዎች 5፡16
ክርስትና ከመመላለስ አይጀምርም፡፡ ክርስትና የሚጀምረው ከመቀመጥ ነው፡፡
በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፡6-7
ክርስትና የሚጀምረው ከሃይል ሳይሆን ከስልጣን ነው፡፡ በሰማያዊ ስፍራ የተቀመጥንበትን የስልጣን ስፍራችንን ስንረዳ ስልጣንን እንረዳለን በእረፍት እንጠቀመዋለን ስራም በመስራት ፍሬም እናፈራለን፡፡
ክርስቶስንም ከሙታን ሲያስነሣው ከአለቅነትና ከሥልጣንም ከኃይልም ከጌትነትም ሁሉ በላይና በዚህ ዓለም ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ሊመጣ ባለው ዓለም ደግሞ ከሚጠራው ስም ሁሉ በላይ በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው በክርስቶስ ባደረገው ሥራ የብርታቱ ጉልበት ይታያል፤ ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛለት ከሁሉ በላይም ራስ እንዲሆን ለቤተ ክርስቲያን ሰጠው። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1፡20-22
መልካሙን ስራ ለማድረግ ተፈጥረናል፡፡ ባዘጋጀልን መልካም ስራ መመላለስ በራስ ጉልበትና ችሎረታ ሳይሆን ከምን ስጦታ ጋር እንተደሰራን ለምን አላማ እንደተፈጠርን ከማወቅ ይጀምራል፡፡
እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፡10
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ክርስቶስ #ጌታ #እረፍት #ቅድሚያ #እምነት #እውቀት #መደገፍ #ሰንበት #በመንፈሴ #በሃይል #በብርታት #ፀጥታ #መመለስ #ማረፍ #ፅድቁን #ኢየሱስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ፀጥታ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መታመን #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment