Popular Posts

Friday, April 19, 2019

ሁሉም ሊፀልየው የሚገባ የፀሎት ርእስ



እግዚአብሔር ሆይ እኔ ልቀየር የማልችላቸውን ነገሮች በዝምታ እንድቀበል ፀጋን ስጠኝ፡፡ እኔ መለወጥ የሚገባኝን ነገር ለመቀየር ድፍረት ስጠኝ፡፡ ልቀይር በምችላቸውና ልቀይር በማልችላቸው በሁለቱ ነገሮች መካከል መለየት እንድችል ጥበብን ስጠኝ፡፡ ሬይንሆልድ ኑይበር
God, give me the grace to accept with serenity the things that cannot be changed, Courage to change the things which should be changed, and the Wisdom to distinguish the one from the other. Reinhold Niebuhr
በህይወት ማድረግ የምንችለቸው ነገሮች አሉ ማድረግ የማንችላቸው ነገሮች ደግሞ አሉ፡፡ ውስን እንደሆንን ሁሉን ነገር ማድረግ እንደማንችል ካልተረዳን  እረፍት በህይወታችን አይመጣም፡፡ በህይወት የሚያርፉና ህይወታቸውን በሚገባ ተደስተውበት የሚያልፉ ሰዎች ማድረግ የሚችሏቸው ታላላቅ ነገሮች እንዳሉ ሁሉ ማድረግ የማይችሉት አንዳንድ ነገር እንዳለ በሚገባ የተረዱ ሰዎች ናቸው፡፡
ማድረግ የምንችለውን ነገር ማወቅ በጣም ወሳኝ እንደመሆኑ መጠን ማድረግ የማንችለውን ነገር ማወቅ ደግሞ እንደሁ ወሳኝ ነው፡፡
በህይወት የሚለወጡና ቢያንስ ለጊዜው የማይለወጡ ነገሮች አሉ፡፡ የሚለወጡ ነገሮችን ማወቅ እንድንለውጣቸው ድፍረት ይሰጠናል፡፡ የማይለወጡ ነገሮችን ማወቅ እንድንታገስ ያስተምረናል፡፡
መለወጥ የማይችለውን ነገር የማያውቅ ሰው መለወጥ በማይችለው ነገር ላይ በከንቱ ጊዜውንና ጉልበቱን ይፈጃል፡፡ መለወጥ የሚችለንውን ነገር የማያውቅ ሰው በከንቱ ተስፋ በመቁረጥ ነገሮችን ሊለውጥ የሚችልበትን በውስጡ ያለውን የተጠራቀመ ጉልበት ሳይጠቀምበት ያባክነዋል፡፡
በወትድርና የበሰለ ወታደር የሚባለው የሚተኩስ ሳይሆን መቼ እንደሚተኩስ የሚያውቅ ሰው ነው፡፡ መቼ መተኮስ እንዳለበት የሚያውቅና መቼ ደግሞ መተኮስ እንደሌለበት የሚያውቅ ወታደር ውጤታማ ወታደር ነው፡፡ የበሰለ ወታደር አንዳንዴ መተኮስ እየቻለ እስከሞት ድረስ በሚያስፈራ ሁኔታ ላላመተኮስ ይታገሳል፡፡
እግዚአብሄር ነገሮችን የምንለውጥበት ጉልበትን ይሰጠናል፡፡ እግዚአብሄር ግን ነገሮችን የምንለውጥበትን ጉልበት ብቻ ሳይሆን የሚሰጠን የማይለወጡትን ነገሮች የምንታገስበትን ፀጋም ይሰጠናል፡፡
አብረንም እየሠራን የእግዚአብሔርን ጸጋ በከንቱ እንዳትቀበሉ ደግሞ እንለምናለን፤ ነገር ግን በሁሉ እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ራሳችንን እናማጥናለን፤ 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6፡1፣4
አንዳንዴ በህይወታችን ያለውን ተራራ ከፊታችን እንድናነሳው ድፍረትን ይሰጠናል ሌላ ጊዜ ደግሞ ተራራውን የምንወጣበት ፀጋን ያበዛልናል፡፡
በእያንዳንዱ የህይወት እርምጃችን እግዚአብሄርን መፈለግ ያለብን በእነዚህ በሁለቱ መካከል ያለውን ልዩነት ለመረዳት ነው፡፡
እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ። ወደ ዕብራውያን 4፡16
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪ #ፀጋ #የሚያስችልሃይል #ብቃት #የእግዚአብሄርችሎታ #ትግስት #የእግዚአብሄርሃይል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ፅድቅ #እግዚአብሄርንመምሰል #ራስንመግዛት #ልብ

No comments:

Post a Comment