Popular Posts

Sunday, April 21, 2019

ይቻላል



ኢየሱስም፦ ቢቻልህ ትላለህ፤ ለሚያምን ሁሉ ይቻላል አለው። የማርቆስ ወንጌል 9፡23
እግዚአብሄር ሁለን ቻይ አምላክ ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሄር መልክና አምሳል ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው ሁለል የሚችለውን እግዚአብሄርን ተከትሎ ሁሉን እንዲችል ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው እግዚአብሄር በምድር ላይ እንዲፈፅም የፈለገውን አላማ ከመፈፀም ምንም ነገር እንዳያግደው ተደርጎ ነው፡፡
ሰው የተፈጠረው የእግዚአብሄር ቃል ታደርጋለህ የሚለውን ሁሉ ማድረግ እንዲችል ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በእምነት የእግዚአብሄርን ሃይል በምድር ላይ እንዲጠቀም ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው እግዚአብሄርን በቃሉ እየተከተል ለሰው የማይቻለውን ነገር እንዲችል ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው እግዚአብሄርን በማመን ለሰው የማይቻለውን ነገር በእምነት እንዲችል ነው፡፡
እምነት የሚመጣው የእግዚአብሄርን ፈቃድ ከማወቅ ነው፡፡ እምነት የሚመጣው የእግዚአብሄርን ፈቃድ አውቆ በመከተል ነው፡፡ እግዚአብሄር ሁሉን እንደሚችል ሁሉ የእግዚአብሄርን ፈቃድ የተረዳ ሰው በእምነት ፈቃዱን ለመፈፀም የማይችለው ነገር አይኖርም፡፡
ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና። የሉቃስ ወንጌል 1፡37
የእግዚአብሄርን ፈቃድ ሊያስቆም የሚችል ምንም ሃይል እንደሌለ ሁሉ የእግዚአብሄርን ፈቃድ የሚከተልን ሰው የሚያቆም ምንም ሃይል የለም፡፡ ለእግዚአብሄር የሚሳነው ነገር እንደሌለ ሁሉ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ከቃሉ አግኝቶ ለሚከተል ሰው የሚሳነው ነገር የለም፡፡
እነሆ፥ እኔ የሥጋ ለባሽ ሁሉ አምላክ እግዚአብሔር ነኝ፤ በውኑ እኔን የሚያቅተኝ ነገር አለን? ትንቢተ ኤርምያስ 32፡27
እግዚአብሄር ፈቃዱን ለመፈፀም የሚያቅተው ነገር እንደሌለ ሁሉ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለሚፈፅም ሰው የሚያቅተው ነገር የለም፡፡
ለሚያምን ሁሉ ይቻላል !
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/AbiyWakumaDinsa/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #መናገር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ቃል #ማሰላሰል #ማድረግ #ሁሉይቻላል #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment