Popular Posts

Tuesday, April 23, 2019

የውስንነት ወሰን


እግዚአብሄር ለክብሩ የፈጠረን የእግዚአብሄር ፍጥረት ነን፡፡ እግዚአብሄር አይወሰንም፡፡ እግዚአብሄር ታላቅ አምላክ እንደሆነ ሁሉ እኛም ልጆቹ የእግዚአብሄር ልጆች ነን፡፡ እግዚአብሄር እንደማይወሰን ታላቅ ሃይሉን የሚያሳየው እኛ በልጆቹ ነው፡፡
እነሆ፥ እኔና እግዚአብሔር የሰጠኝ ልጆች ለእስራኤል በጽዮን ተራራ ከሚኖረው ከሠራዊት ጌታ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምልክትና ተአምራት ነን። ትንቢተ ኢሳይያስ 818
የእግዚአብሄር ሙሉ ድጋፍ ያለን በምንም ነገር የማንወሰን የእግዚአብሄር ህዝቦች ነን፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሄር ሃያል በእኛ ታላቅ ስለሆነ ጠላት ሁልጊዜ ይዋሻል፡፡
እግዚአብሔርን እንዲህ በሉት፦ ሥራህ ግሩም ነው፤ ኃይልህ ብዙ ሲሆን ጠላቶች ዋሹብህ። መዝሙረ ዳዊት 663
እግዚአብሄር ለእኛ ያለው ሙላትና መትረፍረፍ ነው፡፡
እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። የዮሐንስ ወንጌል 10፡10
እግዚአብሄር በውስጣችን ያስቀመጠውን ታላቅ እምቅ ጉልበት እንዳናወጣ የጠላት ተግዳሮት አለብን፡፡ እግዚአብሄር ወደአየልን ታላቅ ደረጃ እንዳንደርስ የሚያስፈራራና የሚያናንቅ ጠላት አለብን፡፡ እግዚአብሄር ያየልንን ሁሉ እንዳንወርስ የሚያጣጥልና የሚያሳንስ ብዙ ነገር በህይወታችን ይገጥመናል፡፡
ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረበት ጊዜ እግዚአብሄር እንዲሰራ የሰጠውን ስራ እንዳይሰራ ሰይጣን ሊያሳንሰውና የሰው ልጆችን ከማዳን ከአላማው ሊያስቆመው ይገዳደረው ነበር፡፡
ፈታኝም ቀርቦ፦ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው። የማቴዎስ ወንጌል 43
አሁንም እግዚአብሄር እንድንሆን ያሰበውን ሁሉ እንዳንሆን እግዚአብሄር አላችሁ የለንን ሁሉ እንዳይኖረን እንዲሁም እግዚአብሄር ታደርጋላችሁ የሚለንን ሁሉ እንዳናደርግ ሰይጣን ሊወስነን ይሰራል፡፡
እግዚአብሄር ወደ አየልን የክብር ቦታ እንዳንሄድ ሰይጣን ሊገድበን ከዚህ ማለፍ አትችልም ብሎ ሊያሳምነን ይጥራል፡፡ የሰይጣንን ውሸት አምነን ከቆምን ከዚያ ሁሉ ብርቱ የጦር መሳሪያችን ጋር እንማረካለን፡፡ የሰይጣንን አታልፉም ግርግር ከሰማነው እግዚአብሄር ወደአለለን ደረጃ ሳንደርስ ከዚያ ሁሉ እምቅ የእግዚአብሄር ሃይል ጋር እናልፋለን፡፡    
የእኛ ወሰን እግዚአብሄር ያየልን እንጂ ሰይጣን የሚለው ውሸት አይደለም፡፡ የእኛ ልክ ሰይጣን የሰፋልን የንቀት ልብስ ሳይሆን እግዚአብሄር ያየልን የክብር ልብስ ነው፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ያድርጉ!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/AbiyWakumaDinsa/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ዘመን #እድል #ዋጁ #ጥበብ #መተርጎም #ገደብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment