Popular Posts

Sunday, April 7, 2019

በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው



የሚጠራጠረው ግን ቢበላ በእምነት ስላልሆነ ተኮንኖአል፤ በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 14፡23
ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሄር ነው፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር ጋር የሚገናኝበት ብቸኛው መንገድ እምነት ነው፡፡ ሰው ካለ እምነት በተፈጥሮ አይን ከማይታየው ከእግዚአብሄር ጋር ምንም ግንኙነት ሊያደርግ አይችልም፡፡ ሰው የተፈጠረበት አላማ በእምነት ከእግዚአብሄር ጋር እንዲኖርና እንዲሰራ ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በእምነት እንዲኖር ነው፡፡
ሰው እምነትን ከጣለ ከእግዚአብሄር ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር አይኖረውም፡፡ እምነት የሌለው ሰው ምንም የስሜት ህዋሳት እንደሌሉት ከማንም ጋር መገናኘትና መግባባት እንደማይችል ሰው ነው፡፡
ሃጢያት ማለት የተፈጠሩበትን አላማ መሳት ማለት ነው፡፡ ሰው ከእምነት ከወጣ የተፈጠረበትን አላማ ይስታል፡፡
ሰው የእግዚአብሄርን አላማ የማይስተው በተፈጥሮ አይን የማይታየውን ሲያይ ብቻ ነው፡፡ ሰው እግዚአብሄርን የሚያስደስተው በተፈጥሮ አይን በሚታየው ነገር ላለመወሰድ ሲወስን ነው፡፡
የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 4፡17-18
ሰው የእግዚአብሄርትን አላማ የማይስተው የልቦናዎቹ አይኖች ሲበሩ ብቻ ነው፡፡
ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1፡18-19
ሰው የእግዚአብሄርን አላማ የማይስተው የእግዚአብሄርን ቃል ሲያምን እና ሲከተል ብቻ ነው፡፡
ሰው ከተፈጠረበት አላማ ዝንፍ የማይለው ሁልጊዜ ታምኖ በእምነት አንጂ በማየት ባለመመላለስ ነው፡፡  
እንግዲህ ሁልጊዜ ታምነን፥ በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና በሥጋ ስናድር ከጌታ ተለይተን በስደት እንዳለን የምናውቅ ከሆንን፥ 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5፡6-7
በእምነት እንድንኖር ታልመን ስለተፈጠረን በእምነት ከምናደርገው ማንኛውም ነገር ውጭ እግዚአብሄርን ማስደሰት አንችልም፡፡ በእምነት የምናደርገው ማንኛውም ነገር እግዚአብሄርን ያስደስተዋል፡፡ በእምነት የምናደርገው ማንኛውም ነገር የተፈጠርንበትን በእምነት የመኖር አላማ መሳት ነው፡፡  
ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ወደ ዕብራውያን 11፡6
ሰው በምድር ላይ ምንም ነገር ቢያደርግ በእምነት ካልሆነ የተፈጠረበትን አላማ መሳት ወይም ሃጢያት ነው፡፡
የሚጠራጠረው ግን ቢበላ በእምነት ስላልሆነ ተኮንኖአል፤ በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 14፡23
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ልብ #ማመን #ቃል #መናገር #ያለእምነት #ስሜት #ሁኔታ #አካባቢ #አላማ #መሳት #ሃጢያት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አለማመን #ጥርጥር #ሁሉይቻላል #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment