Popular Posts

Monday, April 22, 2019

የሚሰራው እግዚአብሄር



ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው፤ እግዚአብሔርም ከጥንት ጀምሮ እስከ ፍጻሜ ድረስ የሠራውን ሥራ ሰው መርምሮ እንዳያገኝ ዘላለምነትን በልቡ ሰጠው። መጽሐፈ መክብብ 3፡11
በህይወታችን ምንም አይነት ትርጕም ያለው ነገር ከሰራን የሰራው እግዚአብሄር ራሱ ነው፡፡ በህይወታችን ትርጉም ያለው ነገር ካቀድን ያቀደው እግዚአብሄር ነው፡፡ በህይወታችን ትርጉም ያለው ነገር ካሰብን መጀመሪያ ያሰበው እግዚአብሄር ራሱ ነው፡፡  
እግዚአብሄር ጀማሪ ነው፡፡ እግዚአብሄር ቀዳሚ ነው፡፡ እግዚአብሄር ከመጀመሪያ ያስባል፡፡ እኛ ከመወለዳችን በፊት ስለእኛ ህይወት አስቦ ጨርሷል፡፡ አለም ከመፈጠሩ በፊት እግዚአብሄር የህይወት እቅዳችንን ሰርቶት ጨርሷል፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ትንቢተ ኤርምያስ 29፡11
እኛ ወደ ምድር ከመምጣታችንና ስራችንን ከመጀመራችን በፊት እግዚአብሄር መጨረሻውን ከመጀመሪያው አይቶታል፡፡  
በመጀመሪያ መጨረሻውን፥ ከጥንትም ያልተደረገውን እነግራለሁ፤ ምክሬ ትጸናለች ፈቃዴንም ሁሉ እፈጽማለሁ እላለሁ። ትንቢተ ኢሳይያስ 46፡10
እኛ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ያደረግነው ጥሩ አሳቢዎች ስለሆንን አይደለም፡፡ የእግዚአብሄርን ፈቃድ በህይወታችን የፈፀምነው ጥሩ ተመራማሪዎች ስለሆንን አይደለም፡፡ የእግዚአብሄር ፈቃድ በህይወታችን የተፈፀመው ምርጥ እቅድ አውጪዎች ስለሆንን አይደለም፡፡
በልባችን መልካም ሃሳብ ካለ እግዚአብሄር አስቀድሞ ያሰበው የራሱ ሃሳብ ነው፡፡ በልባችን መልካም ነገርን ካቀድን እግዚአብሄር የዘላለም እቅዱን በልባችን አካፍሎን ነው፡
በምድር ላይ የሰራነው አንዳች ነገር ቢኖር እግዚአብሄር ሰርቶ የጨረሰውን ብቻ ነው፡፡
ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው፤ እግዚአብሔርም ከጥንት ጀምሮ እስከ ፍጻሜ ድረስ የሠራውን ሥራ ሰው መርምሮ እንዳያገኝ ዘላለምነትን በልቡ ሰጠው። መጽሐፈ መክብብ 311
በሰው ልብ ብዙ አሳብ አለ፤ የእግዚአብሔር ምክር ግን እርሱ ይጸናል። ምሳሌ 1921
በምድር ላይ የምንፀልየው ለእግዚአብሄር ስለህይወት እቅዳችን ሃሳብ ልናቀብለው አይደለም፡፡ የምንፀልየው እግዚአብሄር የህይወት እቅዳችንን እንዲሰራ ሃሳብን ልናካፍለው አይደለም፡፡ የምንፀልየው ስለህይወት እቅዳችን እግዚአብሄርን ልናማክረው አይደለም፡፡ የምንፀልየው ለእግዚአብሄር ሃሳብ ካልሰጠነው የሚረሳ እና የሚዘለል ነገር ስላለና የህይወት እቅዳችን ጎዶሎ ስለሚሆን አይደለም፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ትንቢተ ኤርምያስ 29፡11
ወደ እግዚአብሄር የምንፀልየው እግዚአብሄር ለህይወታችን አስቀድሞ ሰርቶ የጨረሰወን እቅድ ለመረዳትና ከእርሱ ጋር ለመተባበር አብረነው ለመስራት ነው፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #እይታ #አላማ #ተስፋ #ፍፃሜ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ተስፋ #ፍፃሜ #የእግዚአብሄርሃሳብ #የእግዚአብሄርእቅድ #የእግዚአብሄርፈቃድ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment