Popular Posts

Saturday, August 13, 2016

ተዝቆ የማያልቅ የብልፅግና እድል


እግዚአብሄር እጅግ ባለፀጋ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄርን ያየው አንድስ እንኳን የለም በእቅፉ ያለው አንድ ልጁ ተረከው የተባለው እየሱስ ስለእግዚአብሄር ተዝቆ የማያልቅ ብልፅግና ይናገራል፡፡ 
እየሱስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ ሞቷል የሃጢያት እዳችንንም ሙሉ ለሙሉ ከፍሏል፡፡ እየሱስን አንደአዳኝና ጌታችን የተቀበልን ሁላችን ከዚህ የማያልቅ በረከት ተካፋዮች ለመሆን ተጋብዘናል፡፡ እየሱስ በራሱ አንደበት የሚያስተላልፈውን የግብዣ ጥሪ እንስማ፡፡ በመጨረሻ ህይወታችንን መለስ አድርገን ስናይ ከዚህ የማያልቅ በረከት በሚገባ ባለመጠቀማችን እንዳንቆጭ ግብዣውን ለሁላችን ያስተላልፋል፡፡
በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል። ዮሃንስ 15፡7
ይህን የማያልቅ የእግዚአብሄር ሃብት የምንካፈልበትና በዚህ ሃብት የምንኖርበትን መንገድ በቃሉ እንደሆነ ይመሰክራል፡፡ ታላቅ ከሆነውና ባለጠግነቱ ከማይነገረው እግዚአብሄር ጋር የምንገናኘውና የምንያያዘው በቃሉ አማካኝነት ነው፡፡ 
ይህ የእግዚአብሄር ባለጠግነት ወደ እኛ የሚፈስበት መንገዱ ቃሉ በእኛ ውስጥ መኖሩ ነው፡፡ ካለንበት ውስን ከሆነው ሃብት ወጥተን ከያዙል ከውስንነታችንና ከገደባችን ተሻግተረን የዚህ የእግዚአብሄር ባለጠግነት ተካፋይ የምንሆነው በቃሉ አማካኝነት ነው፡፡ 
ቃሉ በእኛ ውስጥ በበዛ ቁጥር የብልፅግና እድላችን ይበዛል፡፡ በቃሉ ስንኖር አስበን የማናውቀው ብልፅግና በቃሉ ውስጥ ተጠውቅልሎ እናገኛለን፡፡ 
ይህ ሁሉ አርነት በክርስቶስ ውስጥ አለ እንዴ ብለን እስከምንገረም ድረስ አስበን ከምናውቀው ሁሉ በላይ ሰፊ የሆነውን የእግዚአብሄርን ባለጠግነት እንለማመዳለን፡፡ 
ይህን ባለጠግነት የምናረጋገጥበትን መንገድ ሲናገር ቃሎቼ በእናንተ ቢኖሩ ይለናል፡፡ ቃሎቹ በእኛ ሲበዙ ይበልጥ የእግዚአብሄር የማያልቅ ብልጥግና ተካፋዮች እንሆናለን፡፡ 
የሚገርመው በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ ብሎ ውጤቱ ምን እንደሚሆን የሚገርምና የሚደንቅ ነገርን ይናገራል፡፡ 
በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል ይላል፡፡ ይህ ማለት ፡- 
ለቃሌ የዋህ ስትሆኑና ስታደርጉት ለቃላችሁና ለፀሎታችሁ የዋህ እሆናለሁ እፈፅመዋለሁ እያለ ነው፡፡ እናንተ ራሳችሁን ስትሰጡኝ እኔ ራሴን እሰጣችሁዋለሁ እያለ ነው፡፡ 
የእኔ ቃል የእናንተ ሲሆን የእኔ ሃብት የእናንተ ይሆናል እያለ ነው፡፡ ቃሎቼን ስታደርጉ ቃላችሁን አደርጋለሁ እያለ ነው፡፡ 
በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል። ዮሃንስ 15፡7 
#ቃል #ብልፅግና #ሃብት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #የእግዚአብሄርቃል #የእግዚአብሔርፈቃድ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment