I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
Name it claim it Take it! “So Jesus answered and said to them, “Have faith in God. For assuredly, I say to you, whoever says to this mount...
-
አንድ አረጋዊ በ ባሕር ዳርቻ መንገድ ላይ እየሄደ እያለ አንድ ወጣት አጎንብሶ የሆነ ነገር በማንሳት ወደ ውቆያኖስ ውስጥ ሲጥል ከሩቅ ያየዋል፡፡ እየተጠጋ ሲሄድ እያነሳ ወደውሃ ውስጥ የሚመልሰው ኮከበ...
-
የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና። የማቴዎስ ወንጌል 22፡14 እግዚአብሄር ቅን ፈራጅ ነው፡፡ እግዚአብሄር እውነተኛ ዳኛ ነው፡፡ እግዚአብሄር ለሁሉም ሰው እኩል እድልን ይሰጣል፡፡ እግዚአብ...
-
እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ክፉውን አትቃወሙ፤ ዳሩ ግን ቀኝ ጉንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ሁሉ ሁለተኛውን ደግሞ አዙርለት፤ ማቴዎስ 5፡39 በህይወቱ የሚያየውን ክፉ ሁሉ በክፉ ለመመለስ የሚያስብ ሰው ...
-
በሃጢያት ጨለማ በጠፋሁ ጊዜ ፈልጎ ያገኘኝን የክርስቶስን እውቀት ብርሃን በልቤ ያበራን እግዚአብሄርን ማመስገን አለብኝ፡፡ ሳላውቀው ሳልረዳው ስለሃጢያቴ የሞተልኝን እግዚአብሄርን የማመስገን ግዴታ አለብኝ፡፡ ከልጅነቴ...
-
የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ፥ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ...
-
ስለኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን እምነት ሲነሳ ስለቅዱሳንና መላእክት ስግደት ፣ ስለማርያም አማላጅነት ስለመሳሰሉት ይነሳል፡፡ ይህ ሁሉ ግን ዋና ነገር አይደለም፡፡ ምንም እንኳን የምናምናቸው መፅሃፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ነገሮች...
-
በሰው ህይወት ውስጥ ግንኙነት እጅግ በጣም አስፈላጊ እንደመሆኑ መጠን ግንኙነት በትክክል እንዲሰራ የሚያስችለው ነዳጁ ፍቅር ነው፡፡ ፍቅር በጣም አስፈላጊ ነገር ቢሆንም ስለፍቅር ብዙ የተባለና የተፃፈ ቢሆንም ...
Friday, June 3, 2016
መዝሙርን ዘፈን ያላደረገው
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዘፈን ሃጢያት ነው ? የሚል ጥያቄ ተነስቶ ብዙዋቻችንን ሲያነጋግር ቆይቶዋል፡፡ እኔም በልቤ ያለውን የሚሰማኝን ዘፈን ሃጢያት ነው በሚል ርእስ ፅሁፍን ፅፌ ነበር፡፡
እግዚአብሄር መዝሙርን እንደሚፈልግ ዘፈንን ግን እንደማይፈልግ እንዲያውም ዘፋኝነት የስጋ ስራ እንደሆነ እነዚህን የሚያደርጉም የእግዚአብሄርን መንግስት እንደማይወርሱ መፅሃፍ ስለዘፈን ጎጂነትር በአፅንኦት ይናገራል፡፡
እግዚአብሄር ዘፈንን ለምን ጠላ መዝሙርንስ ለምን ወደደ? የሚለውን ለመመለስ መዝሙር ከዘፈን የሚለይበትን ነገሮች ማወቅ ግድ ይላል፡፡
መዝሙር እንደ ማንኛውም ዘፈን በግጥም በዜማ የሚሆን እንጉርጉሮ ቢሆንም እንዲሁም መዝሙርንም ዘፈንም የምንጫወትበት መሳሪያ ተመሳሳይ ቢሆንም መዝሙርን ዘፈን የማያደርገው ብዙ ወሳኝ መሰረታዊ ነገሮች አሉት፡፡
መዝሙርን ዘፈን ያላደረገው
1. የመዝሙር አላማ ሰዎች በእግዚአብሄር መልክና አምሳል የተፈጠሩ ክቡራን እንደሆኑና ሰይጣንን ሰምተው በሃጢያት እንዳይዋረዱና ከንቱ እንዳይሆኑ እግዚአብሄር እንደ ፈጠራቸው የክብር ደረጃ እንዲኖሩና ማስተማር ነው፡፡
2. የመዝሙር አላማ ሰዎች እግዚአብሄር በክርስቶስ የከፈለላቸውን የሃጢያት ዋጋ እንዲረዱና ክርስቶስ ለእነርሱ እንደሞተላቸው እነርሱ ደግሞ ለሃጢያት ሞተው ለክርስቶስ እንዲኖሩ የሚያበረታታ ነው፡፡
3. የመዝሙር አላማ ሰዎች የህይወት ጠላት የሆነውን ዲያቢሎስን እና ስራውን ከህይወታቸው እንዲክዱ ልቅነትንና ሃጢያትን እንዲፀየፉ ራስን እንዲገዙ ማበረታታት ነው፡፡
4. የመዝሙር አላማ ሰዎች በጊዜያዊ የአለም ደስታ ዘላለማዊ ህይወታቸውን እንዳያጡ የዘላለም ህይወታቸውን አጥብቀው እንዲይዙ ለማበረታታት የታለመ ነው፡፡
5. የመዝሙር አላማ ሰዎች በምድር ላይ ጊዜያዊ ተላላፊ ምፅአተኛ እንደሆኑ አውቀው በአለም ጉድፍ ራሳቸውን እንዲጠብቁ መምከር ነው፡፡
ወዳጆች ሆይ፥ ነፍስን ከሚዋጋ ሥጋዊ ምኞት ትርቁ ዘንድ እንግዶችና መጻተኞች እንደ መሆናችሁ እለምናችኋለሁ፤1ኛ ጴጥሮስ 2፡11
6. መዝሙር ሰዎች ለፈጠራቸው ባለቤታቸው ለሆነውና ዘወትር ክብር ለሚገባው ለእግዚአብሄር ክብር እንዲሰጡ የሚመራ ነው፡፡
7. መዝሙር እግዚአብሄርን ከምንም በላይ እንዲያከብሩና እርሱን ለማስደሰት እንዲኖሩ የስጋ ምኞታቸውንና የነፍሳቸውን ክፉ ፍላጎት እንቢ እንዲሉ እግዚአብሄርን ለማሳየት የሚዘመር ነው፡፡
8. መዝሙር እንካ በእንካ ያልሆነን ከራስ ወዳድነት የፀዳ ልጁን እየሱስን ለእኛ በመስጠት ያሳየውን የእግዚአብሄርን እውነተኛ ፍቅር የሚገልፅ ነው፡፡
9. እውነተኛ ሰላም የሚገኘው ለእግዚአብሄር አምላክነት ስንገዛና እግዚአብሄ የፈጠረንን አላማ ስንከተል ብቻ እንጂ በተለያየ ቁሳቁስና ልምምድ የማይመጣ መሆኑን የሚያሳይ መዝሙር ነው፡፡
https://www.facebook.com/abiy.wakuma
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment