I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ለተሳካ ህይወትና ለአገልግሎት ራእይ ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ራእይ ከየት እንደመጣን ወዴት እንደምንሄድ ይጠቁመናል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ራእይ ሊጨበጥ የማይችል ሃይማኖታዊ ሃሳብ ብቻ ይመስላቸዋል፡፡ ስለዚህ አንዳንድ ሰዎች...
-
ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱ...
-
የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና! ABIY WAKUMA DINSA BLOG · SATURDAY, 20 AUGUST 2016 ሰው በምድር ላይ እንዲበረክት አለመታበይ አለበት፡፡ ሰው በምድር ላይ ተቋቁሞ...
-
-
It isn’t only what we do in life that matters it is also why we do the things we do. Even our good activities should be checked as in w...
-
በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳ አይሠለጥንብኝም። መብል ለሆድ ነው፥ ሆድም ለመብል ነው፤ እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል። 1 ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6 ፡ 12-13 ...
-
እኛ በጌታ በኢየሱስ አዳኝነት አምነን የዳንን እና የእግዚአብሄር ልጆች የሆንን ሁላችን የአባታችንን እግዚአብሄርን ፍቅር ተካፍለናል፡፡ የእግዚአብሄር ፍቅር በልባችን ፈሷል፡፡ በተሰጠን...
-
Miracle Everyday God created us for a purpose. He is busy working in our lives. We are created for the supernatural. We see God working in ...
Friday, June 3, 2016
መዝሙርን ዘፈን ያላደረገው
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዘፈን ሃጢያት ነው ? የሚል ጥያቄ ተነስቶ ብዙዋቻችንን ሲያነጋግር ቆይቶዋል፡፡ እኔም በልቤ ያለውን የሚሰማኝን ዘፈን ሃጢያት ነው በሚል ርእስ ፅሁፍን ፅፌ ነበር፡፡
እግዚአብሄር መዝሙርን እንደሚፈልግ ዘፈንን ግን እንደማይፈልግ እንዲያውም ዘፋኝነት የስጋ ስራ እንደሆነ እነዚህን የሚያደርጉም የእግዚአብሄርን መንግስት እንደማይወርሱ መፅሃፍ ስለዘፈን ጎጂነትር በአፅንኦት ይናገራል፡፡
እግዚአብሄር ዘፈንን ለምን ጠላ መዝሙርንስ ለምን ወደደ? የሚለውን ለመመለስ መዝሙር ከዘፈን የሚለይበትን ነገሮች ማወቅ ግድ ይላል፡፡
መዝሙር እንደ ማንኛውም ዘፈን በግጥም በዜማ የሚሆን እንጉርጉሮ ቢሆንም እንዲሁም መዝሙርንም ዘፈንም የምንጫወትበት መሳሪያ ተመሳሳይ ቢሆንም መዝሙርን ዘፈን የማያደርገው ብዙ ወሳኝ መሰረታዊ ነገሮች አሉት፡፡
መዝሙርን ዘፈን ያላደረገው
1. የመዝሙር አላማ ሰዎች በእግዚአብሄር መልክና አምሳል የተፈጠሩ ክቡራን እንደሆኑና ሰይጣንን ሰምተው በሃጢያት እንዳይዋረዱና ከንቱ እንዳይሆኑ እግዚአብሄር እንደ ፈጠራቸው የክብር ደረጃ እንዲኖሩና ማስተማር ነው፡፡
2. የመዝሙር አላማ ሰዎች እግዚአብሄር በክርስቶስ የከፈለላቸውን የሃጢያት ዋጋ እንዲረዱና ክርስቶስ ለእነርሱ እንደሞተላቸው እነርሱ ደግሞ ለሃጢያት ሞተው ለክርስቶስ እንዲኖሩ የሚያበረታታ ነው፡፡
3. የመዝሙር አላማ ሰዎች የህይወት ጠላት የሆነውን ዲያቢሎስን እና ስራውን ከህይወታቸው እንዲክዱ ልቅነትንና ሃጢያትን እንዲፀየፉ ራስን እንዲገዙ ማበረታታት ነው፡፡
4. የመዝሙር አላማ ሰዎች በጊዜያዊ የአለም ደስታ ዘላለማዊ ህይወታቸውን እንዳያጡ የዘላለም ህይወታቸውን አጥብቀው እንዲይዙ ለማበረታታት የታለመ ነው፡፡
5. የመዝሙር አላማ ሰዎች በምድር ላይ ጊዜያዊ ተላላፊ ምፅአተኛ እንደሆኑ አውቀው በአለም ጉድፍ ራሳቸውን እንዲጠብቁ መምከር ነው፡፡
ወዳጆች ሆይ፥ ነፍስን ከሚዋጋ ሥጋዊ ምኞት ትርቁ ዘንድ እንግዶችና መጻተኞች እንደ መሆናችሁ እለምናችኋለሁ፤1ኛ ጴጥሮስ 2፡11
6. መዝሙር ሰዎች ለፈጠራቸው ባለቤታቸው ለሆነውና ዘወትር ክብር ለሚገባው ለእግዚአብሄር ክብር እንዲሰጡ የሚመራ ነው፡፡
7. መዝሙር እግዚአብሄርን ከምንም በላይ እንዲያከብሩና እርሱን ለማስደሰት እንዲኖሩ የስጋ ምኞታቸውንና የነፍሳቸውን ክፉ ፍላጎት እንቢ እንዲሉ እግዚአብሄርን ለማሳየት የሚዘመር ነው፡፡
8. መዝሙር እንካ በእንካ ያልሆነን ከራስ ወዳድነት የፀዳ ልጁን እየሱስን ለእኛ በመስጠት ያሳየውን የእግዚአብሄርን እውነተኛ ፍቅር የሚገልፅ ነው፡፡
9. እውነተኛ ሰላም የሚገኘው ለእግዚአብሄር አምላክነት ስንገዛና እግዚአብሄ የፈጠረንን አላማ ስንከተል ብቻ እንጂ በተለያየ ቁሳቁስና ልምምድ የማይመጣ መሆኑን የሚያሳይ መዝሙር ነው፡፡
https://www.facebook.com/abiy.wakuma
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment