በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፡፡ ምሳሌ 3፡5
ህይወት የእግዚአብሄር ውድ ስጦታ ነው፡፡ ይህን ስጦታ በሚገባ መያዝና መጠቀም ማስተዋል ይጠይቃል፡፡ የህይወትን
ስጦታ በሚገባ ለመጠቀም ወደ ሰጭው መመለስና ለምን እንደሰጠንና ምን እንድናደርግበት እንደሰጠን መረዳት ይጠይቃል፡፡
በሌላ አነጋገር በምድር ላይ ለእግዚአብሄር ክብር ለመኖር ሁልጊዜ በእግዚአብሄር ምሪት ላይ መደገፍ ይጠበቅብናል፡፡
የእግዚአብሄርን ስጦታ ህይወትን በራስህ ማስተዋል አትኖረውም፡፡ የእግዚአብሄርን የህይወት ስጦታ በእግዚአብሄር እውቀትና ምሪት መጠቀም ይጠይቃል፡፡
ሁል ጊዜ በራሳችን እውቀትና ማስተዋል ነገሮችን ለማድረግ እንፈተናለን፡፡ ነገር ግን የራሳችን ማስተዋል ያስተናል እንጂ የትም አያደርሰንም፡፡
አሳቤ እንደ አሳባችሁ መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና ይላል እግዚአብሔር፦ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው። ኢሳያስ 55፡8-9
በእግዚአብሄር የምትታመነውና የምትደገፈው ለእግዚአብሄር አዋቂነትና ፍፁም መሪነትና እውቅና በመስጠት ነው፡፡ ይህን በማለት ለእግዚአብሄር እውቅና ልንሰጥ ይገባናል፡፡
• እኔ ከመፈጠሬ በፊት ለእኔ ያቀድከው ሃሳብ አለ
• የእኔ የህይወት እቅድና ንድፍ በአንተ ዘንድ አለ
• እኔ ለራሴ ከማውቀው በላይ አንተ ለእኔ ታውቃለህ
• አንተ ለእኔ ያለህ አላማ የፍቅር አላማ ነው
• አንተ ለእኔ የምታስበው ሃሳብ መልካም ብቻ ነው
በማለት ይህንን እግዚአብሄር ለህይወታችን ያለውን ሃሳብ ከእግዚአብሄር መፈለግና መከተል መንገዳችን እንዲቃና ያደርጋል፡፡
ምሳሌ 3፡6 በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል።
ለተጨማሪ ፅሁፎች
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና . . . ማቴዎስ 28፡18 በመጀመሪያ ሰው ከሙሉ ስልጣን ጋር ተፈጥሮ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ ...
-
የማቴዎስ ወንጌል 22:1-14 1 ኢየሱስም መለሰ ደግሞም በምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ፦ 2 መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች። 3 የታደሙትንም ወደ ሰር...
-
ኢየሱስ ወደምድር የመጣው በስጋ ነው፡፡ ኢየሱስ የመጣው ከሰው ልጅ ተወልዶ ሰው ሆኖ ነው፡፡ ኢየሱስ ሰው ሆኖ የመጣው በሰው የተሰራውን ሃጢያት በሰውነት ለመክፈል ነው፡፡ እንግዲህ በአንድ በደል ምክንያት ፍ...
-
የዲያቢሎስ አላማ አንድና አንድ ነው፡፡ ዲያቢሎስ ከመጣ ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ለሌላ ነገር አይመጣም፡፡ ዲያቢሎስንብ የመጋዣው መንገድ ደግሞ በእግዚአብሄር ላይ ማመፅ ወደ እግዚአብሄር...
-
ክርስቲያናዊ ደስታን አፈላለግ በሚቀጥሉት አምስት እምነቶች ላይ የተገነባ የህይወት መረዳት ነው፡፡ l. ደስተኛ ለመሆን መጓጓት አለም አቀፋዊ ሁለንተናዊ የሰዎች ምኞት ነው፡፡ ደስተኛ ለመሆ...
-
የፈጠረን እግዚአብሄር ሁለንተናችንን ያውቃል፡፡ እግዚአብሄር በውጫዊ ነገራችን አይወሰድም፡፡ እግዚአብሄር ፊትን አያየም፡፡ እግዚአብሄር የፊትን መልክ አይቶ አይሳብም፡፡ እግዚአብሄር ቁመናችንን አይቶ አይደነቅም፡፡...
-
እግዚአብሄር የፈጠረን በመልኩና በአምሳሉ ነው፡፡ እግዚአብሄርን በምድር ላይ የፈጠረን በባህሪው እግዚአብሄርን በምድር ላይ እንድንወክለው ነው፡፡ እግዚአብሄር በኢየሱስ የመስቀል ስራ የሃጢያት እዳችንን ሁሉ ሲከፍ...
-
ከከንቱ ኑሮአችንም የተገዛነው እና የተዋጀነው በክርስቶስ ደም ነው፡፡ ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደ ሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክ...
-
እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥...
No comments:
Post a Comment