በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፡፡ ምሳሌ 3፡5
ህይወት የእግዚአብሄር ውድ ስጦታ ነው፡፡ ይህን ስጦታ በሚገባ መያዝና መጠቀም ማስተዋል ይጠይቃል፡፡ የህይወትን
ስጦታ በሚገባ ለመጠቀም ወደ ሰጭው መመለስና ለምን እንደሰጠንና ምን እንድናደርግበት እንደሰጠን መረዳት ይጠይቃል፡፡
በሌላ አነጋገር በምድር ላይ ለእግዚአብሄር ክብር ለመኖር ሁልጊዜ በእግዚአብሄር ምሪት ላይ መደገፍ ይጠበቅብናል፡፡
የእግዚአብሄርን ስጦታ ህይወትን በራስህ ማስተዋል አትኖረውም፡፡ የእግዚአብሄርን የህይወት ስጦታ በእግዚአብሄር እውቀትና ምሪት መጠቀም ይጠይቃል፡፡
ሁል ጊዜ በራሳችን እውቀትና ማስተዋል ነገሮችን ለማድረግ እንፈተናለን፡፡ ነገር ግን የራሳችን ማስተዋል ያስተናል እንጂ የትም አያደርሰንም፡፡
አሳቤ እንደ አሳባችሁ መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና ይላል እግዚአብሔር፦ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው። ኢሳያስ 55፡8-9
በእግዚአብሄር የምትታመነውና የምትደገፈው ለእግዚአብሄር አዋቂነትና ፍፁም መሪነትና እውቅና በመስጠት ነው፡፡ ይህን በማለት ለእግዚአብሄር እውቅና ልንሰጥ ይገባናል፡፡
• እኔ ከመፈጠሬ በፊት ለእኔ ያቀድከው ሃሳብ አለ
• የእኔ የህይወት እቅድና ንድፍ በአንተ ዘንድ አለ
• እኔ ለራሴ ከማውቀው በላይ አንተ ለእኔ ታውቃለህ
• አንተ ለእኔ ያለህ አላማ የፍቅር አላማ ነው
• አንተ ለእኔ የምታስበው ሃሳብ መልካም ብቻ ነው
በማለት ይህንን እግዚአብሄር ለህይወታችን ያለውን ሃሳብ ከእግዚአብሄር መፈለግና መከተል መንገዳችን እንዲቃና ያደርጋል፡፡
ምሳሌ 3፡6 በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል።
ለተጨማሪ ፅሁፎች
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ለተሳካ ህይወትና ለአገልግሎት ራእይ ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ራእይ ከየት እንደመጣን ወዴት እንደምንሄድ ይጠቁመናል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ራእይ ሊጨበጥ የማይችል ሃይማኖታዊ ሃሳብ ብቻ ይመስላቸዋል፡፡ ስለዚህ አንዳንድ ሰዎች...
-
ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱ...
-
የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና! ABIY WAKUMA DINSA BLOG · SATURDAY, 20 AUGUST 2016 ሰው በምድር ላይ እንዲበረክት አለመታበይ አለበት፡፡ ሰው በምድር ላይ ተቋቁሞ...
-
-
It isn’t only what we do in life that matters it is also why we do the things we do. Even our good activities should be checked as in w...
-
በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳ አይሠለጥንብኝም። መብል ለሆድ ነው፥ ሆድም ለመብል ነው፤ እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል። 1 ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6 ፡ 12-13 ...
-
እኛ በጌታ በኢየሱስ አዳኝነት አምነን የዳንን እና የእግዚአብሄር ልጆች የሆንን ሁላችን የአባታችንን እግዚአብሄርን ፍቅር ተካፍለናል፡፡ የእግዚአብሄር ፍቅር በልባችን ፈሷል፡፡ በተሰጠን...
-
Miracle Everyday God created us for a purpose. He is busy working in our lives. We are created for the supernatural. We see God working in ...
No comments:
Post a Comment