በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፡፡ ምሳሌ 3፡5
ህይወት የእግዚአብሄር ውድ ስጦታ ነው፡፡ ይህን ስጦታ በሚገባ መያዝና መጠቀም ማስተዋል ይጠይቃል፡፡ የህይወትን
ስጦታ በሚገባ ለመጠቀም ወደ ሰጭው መመለስና ለምን እንደሰጠንና ምን እንድናደርግበት እንደሰጠን መረዳት ይጠይቃል፡፡
በሌላ አነጋገር በምድር ላይ ለእግዚአብሄር ክብር ለመኖር ሁልጊዜ በእግዚአብሄር ምሪት ላይ መደገፍ ይጠበቅብናል፡፡
የእግዚአብሄርን ስጦታ ህይወትን በራስህ ማስተዋል አትኖረውም፡፡ የእግዚአብሄርን የህይወት ስጦታ በእግዚአብሄር እውቀትና ምሪት መጠቀም ይጠይቃል፡፡
ሁል ጊዜ በራሳችን እውቀትና ማስተዋል ነገሮችን ለማድረግ እንፈተናለን፡፡ ነገር ግን የራሳችን ማስተዋል ያስተናል እንጂ የትም አያደርሰንም፡፡
አሳቤ እንደ አሳባችሁ መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና ይላል እግዚአብሔር፦ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው። ኢሳያስ 55፡8-9
በእግዚአብሄር የምትታመነውና የምትደገፈው ለእግዚአብሄር አዋቂነትና ፍፁም መሪነትና እውቅና በመስጠት ነው፡፡ ይህን በማለት ለእግዚአብሄር እውቅና ልንሰጥ ይገባናል፡፡
• እኔ ከመፈጠሬ በፊት ለእኔ ያቀድከው ሃሳብ አለ
• የእኔ የህይወት እቅድና ንድፍ በአንተ ዘንድ አለ
• እኔ ለራሴ ከማውቀው በላይ አንተ ለእኔ ታውቃለህ
• አንተ ለእኔ ያለህ አላማ የፍቅር አላማ ነው
• አንተ ለእኔ የምታስበው ሃሳብ መልካም ብቻ ነው
በማለት ይህንን እግዚአብሄር ለህይወታችን ያለውን ሃሳብ ከእግዚአብሄር መፈለግና መከተል መንገዳችን እንዲቃና ያደርጋል፡፡
ምሳሌ 3፡6 በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል።
ለተጨማሪ ፅሁፎች
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
በክርስትና ለቤተክርስቶን ከተሰጡ አገልግሎቶች መካከል ትንቢት አንዱ ነው፡፡ ትንቢት የሚመጣው ለማነጽና ለመምከር ለማጽናናትም ነው፡፡ ትንቢትን የሚናገር ግን ለማነጽና ለመምከር ለማጽናናትም ለሰው ይናገራል። 1...
-
Then Peter opened his mouth, and said, Of a truth I perceive that God is no respecter of persons: Acts 10:34 God isn’t a respecter...
-
We all come across disappointments. We may face situations that we have never dreamed of facing them one day. We may face something we t...
-
እንደ ፍቅር በጣም አስፈላጊ ነገር የለም፡፡ እንደ ፍቅር ደግሞ ትርጉሙ የተዛባ ነገር በአለም ላይ ምንም ነገር የለም፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ፍቅር የሚሉት ምኞታቸውን ነው፡፡ የፍቅርንና የምኞትን ባህሪያት ከእግዚአብሄር ቃ...
-
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ከእርሱ ጋር ህብረት ማድረግ ፈልጎ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን በመልኩና በአምሳሉ የፈጠረው ህብረታቸው የተሳካ እንዲሆን ነው፡፡ ሰው በሃጢያት ከመውደቁ በፊት ከእግዚአብሄ ጋር የተሳካ ህብ...
-
ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ፦ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድን...
-
ማሪያም ታማልዳለች ወይስ አታማልድም የሚለው ጥያቄ በኢትዮጲያ ውስጥ ብዙ ክርክርን ሲያስነሳ የቆየ ጥያቄ ነው፡፡ አንዳንዶች ማሪያም በምድር ላይ እያለች አማልዳለች ነገር ግን ከሞተች በኃላ ማማለድ አትችልም ብለው...
-
We want God to use us mightily. We ask God “use me and I will do whatever it takes”. When the time to pay the price that isn’t expected...
-
መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና፤ ኤፌሶን 5፡18 የእግዚአብሄርን ነገር በመንፈስ ነው የሚሰራው፡፡ የተለያዩ ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ እንችላለን ካለ መንፈስ ሙላትና እ...
-
ሰዎችን የሚማርኳቸውና የሚደሰቱባቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ካለ እምነት ግን እግዚአብሄርን ደስ ማሰኘት አይቻልም፡፡ ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ ...

No comments:
Post a Comment