Popular Posts

Sunday, September 15, 2019

የሌለኝ ሁሉ የማያስፈልገኝ ነው



እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። መዝሙረ ዳዊት 23፡1
የሌለኝ የማያስፈልገኝ እንደሆነ በትክክል ለመረዳት አመታት ሊፈጅብኝ ይችላል፡፡ የሌለኝ የማያስፈልገኝ እንደሆነ ሙሉ ለሙሉ ለመረዳት ጌታ መጥቶ አሁን በድንግዝግዝ የማየውን በግልፅ ላየው ይገባ ይሆናል፡፡ እውነቱ ግን የሌለኝ የማያስፈልገኝ ነው፡፡
እግዚአብሄር እረኛዬ ነው የሚያሳጣኝ የለም እያልኩ የሚያስፈልገኝን አጣሁ ማለት አልችልም፡፡ የሌለኝ የማያስፈልገኝ ነው፡፡
የሌለኝ የማያስፈልገኝ እንደሆነ ለአእምሮዬ ሊከብድ ይችላል፡፡ እውነቱ ግን የሚያስፈልገኝን ሁሉ የሰጠኝ እግዚአብሄር ያልሰጠኝን ያልሰጠኝ ስለማያስፈልግኝ ብቻ ነው፡፡
እኔ ራሴን አልፈጠርኩትም፡፡ የፈጠረኝ እግዚአብሄር ነው፡፡ የሰራኝ እርሱ ነው፡፡ እርሱ ሁለንተናዬን ያውቃል፡፡ እርሱ እንደ መልካም እረኛ ያልሰጠኝ ነገር ካለ የማያስፈልገኝ ነገር መሆን አለበት፡፡
አቤቱ፥ መረመርኸኝ፥ አወቅኸኝም። አንተ መቀመጤንና መነሣቴን አወቅህ፤ አሳቤን ሁሉ ከሩቅ አስተዋልህ። ፍለጋዬንና ዕረፍቴን አንተ መረመርህ፤ መንገዶቼን ሁሉ ቀድመህ አወቅህ፥ መዝሙረ ዳዊት 139፡1-3
እግዚአብሄር ምን እንደሚያስፈለገን ያውቃል፡፡ ከእኛ በላይ እግዚአብሄር ለእኛ ያውቃል፡፡ እፃ የሚያስፈልገንን ለማግኘት ከምንፈልገው በላይ እግዚአብሄር የሚያስፈልገንን ለማሟላት ይፈልጋል፡፡
ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። የማቴዎስ ወንጌል 6፡32
የሚያስፈልገኝን አጣሁ ከማለት ይልቅ የሌለኝ የማያስፈልገኝ ነው ማለት ይቀላል፡፡
እግዚአብሄ እረኛዬ ሆኖ የሚያስፈልገኝን አሳጣኝ ከምል ይልቅ የሌለኝ የማያስፈልገኝ ነው ብል አልሳሳትም፡፡
ወይስ ከእናንተ፥ ልጁ እንጀራ ቢለምነው፥ ድንጋይን የሚሰጠው ከእናንተ ማን ሰው ነው? ዓሣስ ቢለምነው እባብን ይሰጠዋልን? እንኪያስ እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠትን ካወቃችሁ፥ በሰማያት ያለው አባታችሁ ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መልካም ነገርን ይሰጣቸው? የማቴዎስ ወንጌል 7፡9-11
እግዚአብሄር መልካም ሆኖ በትእቢት የሚያስፈልገኝን አሳጣኝ ከምል የሌለኝ የማያስፈልገኝ ነው ብል እውነተኛ ትህትና ነው፡፡
እግዚአብሄር እረኛዬ ሆኖ የሚያስፈልገኝን አሳጣኝ ብዬ ከምጠራጠር የሌለኝ የማያስፈልገኝ ነው ብዬ ማመን ይሻለኛል፡፡ እግዚአብሄር ከፍቅሩ የተነሳ ኢየሱስን እንዲሞትልኝ አሳልፎ እስኪሰጠኝ ወዶኝ ሌላውን ጥቃቅኑን ያነሰውን ነገርማ እንዴት አይሰጠፅም ብዬ ልመን?  የሚያስፈልገኝ ጎድሎብኛል ብዬ ከማመን አንድ ልጁን ሳይሳሳ የሰጠኝ እግዚአብሄር ሌላውንማ አብልጦ ይሰጠኛል ብዬ ማመን ይቀርበኛል፡፡
ለገዛ ልጁ ያልራራለት ነገር ግን ስለ ሁላችን አሳልፎ የሰጠው ያው ከእርሱ ጋር ደግሞ ሁሉን ነገር እንዲያው እንዴት አይሰጠንም? ወደ ሮሜ ሰዎች 8፡32
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #እረኛ #አላማ #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ጥሪ #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment