| 
   
መዝሙረ
  ዳዊት 136 
 | 
 ||
| 
   
እግዚአብሔርን
  አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና። 
 | 
  ||
| 
   
የአማልክትን
  አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና። 
 | 
  ||
| 
   
የጌቶችን
  ጌታ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
እርሱ
  ብቻውን ታላቅ ተኣምራትን ያደረገ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ሰማያትን
  በብልሃት የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ምድርን
  በውኃ ላይ ያጸና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ብቻውን
  ታላላቅ ብርሃናትን የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ለፀሐይ
  ቀንን ያስገዛው፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ለጨረቃና
  ለከዋክብትም ሌሊትን ያስገዛቸው፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ከበኵራቸው
  ጋር ግብጽን የመታ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
እስራኤልንም
  ከመካከላቸው ያወጣ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
በጸናች
  እጅ በተዘረጋችም ክንድ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
የኤርትራን
  ባሕር በየክፍሉ የከፈለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
እስራኤልን
  በመካከሉ ያሳለፈ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ፈርዖንንና
  ሠራዊቱን በኤርትራ ባሕር የጣለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ሕዝቡን
  በምድረ በዳ የመራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ታላላቅ
  ነገሥታትን የመታ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ብርቱዎችንም
  ነገሥታት የገደለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
የአሞራውያንን
  ንጉሥ ሴዎንን፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
የባሳንን
  ንጉሥ ዐግን፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ምድራቸውን
  ርስት አድርጎ የሰጠ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ለባሪያው
  ለእስራኤል ርስት፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና። 
 | 
  ||
| 
   
እኛን
  በመዋረዳችን አስቦናልና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ 
 | 
  ||
| 
   
ከጠላቶቻችንም
  እጅ አድኖናልና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና 
 | 
  ||
| 
   
ለሥጋ
  ሁሉ ምግብን የሚሰጥ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና። 
 | 
  ||
| 
   
የሰማይን
  አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና። 
 | 
  ||
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
- 
Live soberly and be vigilant, for the devil, who is not your partner, prowls around like a roaring lion looking for someone to devour. Re...
 - 
ኢየሱስ ለእኛ ሰው ሆኖ ወደምርድ ስለመጣ ፍፁም ምሳሌያችን ነው፡፡ ማንንም ባንከተል ኢየሱስን መከተል አለብን፡፡ ማንም ምንም የሚጎድለው ባህሪ ቢኖር ኢየሱስ በባህሪው ፍፁም ነው፡፡ ኢየሱስ ሙሉ ለሙሉ ልንከተለው የምንች...
 - 
by John Greenleaf Whittier When things go wrong as they sometimes will, When the road you're trudging seems all uphill, When th...
 - 
ነቢይ የእግዚአብሄር አፍ ነው፡፡ ነቢይ ከለአግዚአብሄር ሰምቶ የሚናገር ነው፡፡ ነቢይ የእግዚእብህር በልቡና ያለውን ተረድቶ ለህዝቡ የሚገልፅ ነው፡፡ በድሮ ዘመን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሄር ነቢይን በዚህ በእኛ ዘመን ...
 - 
There is nothing sweeter than living a simple life that can be mange properly. That is why the bible tells us to simplify our lives. Seein...
 - 
ዳሩ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እናገራለሁ፤ ዘመኑ አጭር ሆኖአል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሚስቶች ያሉአቸው እንደሌላቸው ይሁኑ፥ 1 ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 7 ፡ 29 የትዳር አላማ አንዱ ...
 - 
እኛ በክርስቶስ ኢየሱስ አዳኝነት አምነን የዳንን ሁላችን እግዚአብሄር በምድር ላይ ለሰጠን የቤት ስራ በእግዚአብሄር መንፈስ ተቀብተናል፡፡ ካለ እግዚአብሄር መንፈስ እርዳታ የእግዚአብሄርን ስራ መስራት አይቻልም፡፡ የእ...
 
Monday, September 9, 2019
ምሕረቱ ለዘላለም ነውና
Subscribe to:
Post Comments (Atom)

No comments:
Post a Comment