መዝሙረ
ዳዊት 136
|
||
እግዚአብሔርን
አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
የአማልክትን
አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
የጌቶችን
ጌታ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
እርሱ
ብቻውን ታላቅ ተኣምራትን ያደረገ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ሰማያትን
በብልሃት የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ምድርን
በውኃ ላይ ያጸና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ብቻውን
ታላላቅ ብርሃናትን የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ለፀሐይ
ቀንን ያስገዛው፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ለጨረቃና
ለከዋክብትም ሌሊትን ያስገዛቸው፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ከበኵራቸው
ጋር ግብጽን የመታ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
እስራኤልንም
ከመካከላቸው ያወጣ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
በጸናች
እጅ በተዘረጋችም ክንድ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
የኤርትራን
ባሕር በየክፍሉ የከፈለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
እስራኤልን
በመካከሉ ያሳለፈ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ፈርዖንንና
ሠራዊቱን በኤርትራ ባሕር የጣለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ሕዝቡን
በምድረ በዳ የመራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ታላላቅ
ነገሥታትን የመታ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ብርቱዎችንም
ነገሥታት የገደለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
የአሞራውያንን
ንጉሥ ሴዎንን፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
የባሳንን
ንጉሥ ዐግን፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ምድራቸውን
ርስት አድርጎ የሰጠ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ለባሪያው
ለእስራኤል ርስት፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
እኛን
በመዋረዳችን አስቦናልና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
ከጠላቶቻችንም
እጅ አድኖናልና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና
|
||
ለሥጋ
ሁሉ ምግብን የሚሰጥ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
የሰማይን
አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
So if the Son sets you free, you will be free indeed. John 8:36 Mankind isn’t designed for any kinds of bondage. God created ma...
-
ፍቅር አስደናቂ ነው፡፡ በተለይ ፍቅር ሁሉን ያምናል የሚለውን ቃል ሳሰላስል ነበር ያመሸሁት፡፡ ይህን ቃል ሳሰላስል ጌታ የሰጠኝን መረዳት አብሬያችሁ ልካፈል ወደድኩ፡፡ ፍቅር ሁሉን ያምናል፡፡ 1ኛ ቆሮንጦስ ...
-
ኢየሱስ ወደምድር የመጣው በስጋ ነው፡፡ ኢየሱስ የመጣው ከሰው ልጅ ተወልዶ ሰው ሆኖ ነው፡፡ ኢየሱስ ሰው ሆኖ የመጣው በሰው የተሰራውን ሃጢያት በሰውነት ለመክፈል ነው፡፡ እንግዲህ በአንድ በደል ምክንያት ፍ...
-
ሰው ደስ ከሚለውና በሕይወቱ ሳለ መልካምን ነገር ከሚያደርግ በቀር መልካም ነገር እንደሌለ አወቅሁ። ደግሞም ሰው ሁሉ ይበላና ይጠጣ ዘንድ በድካሙም ሁሉ ደስ ይለው ዘንድ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው። ከሚበላውና ከሚጠጣው ደስም...
-
ዲሞክራሲ ትልቅ ሃላፊነት ነው፡፡ ዲሞክራሲ የሚደግፈንን ሰው መደገፍ ብቻ አይደለም፡፡ ዲሞክራሲ የሚቃወመንን መቀበል ነው፡፡ ዲሞክራሲ ከእኛ የተለየ ሃሳብ ያለውን ሰው ስፍራ መስጠት ማክበር ነው፡፡ ሰሞኑን ለዶክተር ...
-
የዲያቢሎስ አላማ አንድና አንድ ነው፡፡ ዲያቢሎስ ከመጣ ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ለሌላ ነገር አይመጣም፡፡ ዲያቢሎስንብ የመጋዣው መንገድ ደግሞ በእግዚአብሄር ላይ ማመፅ ወደ እግዚአብሄር...
-
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ኤርምያስ 29፡11 እግዚአብሄር እኛን የፈጠረው በአላማ ነው፡፡ ለእግ...
-
ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ዮሃንስ 14፡27 ነገር ግን እኛ ነን ሰላማችንን የመጠበቅ ሃላፊነት ያለብን ፡፡ ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ እኛ ይ...
-
የፈጠረን እግዚአብሄር ሁለንተናችንን ያውቃል፡፡ እግዚአብሄር በውጫዊ ነገራችን አይወሰድም፡፡ እግዚአብሄር ፊትን አያየም፡፡ እግዚአብሄር የፊትን መልክ አይቶ አይሳብም፡፡ እግዚአብሄር ቁመናችንን አይቶ አይደነቅም፡፡...
-
10-11 በመንፈስም ወደ ታላቅና ወደ ረጅም ተራራ ወሰደኝ፥ የእግዚአብሔርም ክብር ያለባትን ቅድስቲቱን ከተማ ኢየሩሳሌምን ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስትወርድ አሳየኝ፤ ብርሃንዋም እጅግ ...
Monday, September 9, 2019
ምሕረቱ ለዘላለም ነውና
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment