|
መዝሙረ
ዳዊት 136
|
||
|
እግዚአብሔርን
አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
የአማልክትን
አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
የጌቶችን
ጌታ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
እርሱ
ብቻውን ታላቅ ተኣምራትን ያደረገ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ሰማያትን
በብልሃት የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ምድርን
በውኃ ላይ ያጸና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ብቻውን
ታላላቅ ብርሃናትን የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ለፀሐይ
ቀንን ያስገዛው፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ለጨረቃና
ለከዋክብትም ሌሊትን ያስገዛቸው፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ከበኵራቸው
ጋር ግብጽን የመታ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
እስራኤልንም
ከመካከላቸው ያወጣ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
በጸናች
እጅ በተዘረጋችም ክንድ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
የኤርትራን
ባሕር በየክፍሉ የከፈለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
እስራኤልን
በመካከሉ ያሳለፈ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ፈርዖንንና
ሠራዊቱን በኤርትራ ባሕር የጣለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ሕዝቡን
በምድረ በዳ የመራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ታላላቅ
ነገሥታትን የመታ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ብርቱዎችንም
ነገሥታት የገደለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
የአሞራውያንን
ንጉሥ ሴዎንን፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
የባሳንን
ንጉሥ ዐግን፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ምድራቸውን
ርስት አድርጎ የሰጠ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ለባሪያው
ለእስራኤል ርስት፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
እኛን
በመዋረዳችን አስቦናልና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ከጠላቶቻችንም
እጅ አድኖናልና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና
|
||
|
ለሥጋ
ሁሉ ምግብን የሚሰጥ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
የሰማይን
አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
በአለማችን ላይ እውነተኛ ደቀመዛሙርቶች አሉ፡፡ የስም ብቻ ደቀመዛሙርቶች ደግሞ አሉ፡፡ እውነተኛ ደቀመዝሙር የሚያደርገን ምን እንደሆነ ማወቅ በጣም ወሳኝ ነገር ነው፡፡ የእውነተኛ ደቀመዝሙርነት መንገድ ላይ መሆናችንን ...
-
እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ...
-
https://youtu.be/VhF0pSsp14I በቃልኪዳን መነጽር ህይወታችን ማየት አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa ሬማ እምነት አገልግሎት በርሚንግሃም ቤተክርስትያን
-
Live soberly and be vigilant, for the devil, who is not your partner, prowls around like a roaring lion looking for someone to devour. Re...
-
ተጠማው እልውናህን መገኘትህን ጌታ ድምጽህን መዓዛ ግርማህን አልፈልግም ኖረ ኖረ ኖረ ሞተ አልፈልግም መሆን በምድር የታመነ መንፈስክን ይዞ ይዞ ሚገሰግስ ለተጠማው ደርሶ የልብህን የሚያደር...
-
Bait your hook an' keep a- tryin '-- Keep a-goin '! When the weather kills your crop, Keep a-goin '! Though 'tis...
-
ነቢይ የእግዚአብሄር አፍ ነው፡፡ ነቢይ ከለአግዚአብሄር ሰምቶ የሚናገር ነው፡፡ ነቢይ የእግዚእብህር በልቡና ያለውን ተረድቶ ለህዝቡ የሚገልፅ ነው፡፡ በድሮ ዘመን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሄር ነቢይን በዚህ በእኛ ዘመን ...
-
የወርቅ ቀለበት በእርያ አፍንጫ እንደ ሆነ፥ ከጥበብ የተለየች ቆንጆ ሴትም እንዲሁ ናት። መጽሐፈ ምሳሌ 11፡22 የኛውም ወርቅ እርያን አንደማያሳምረው ሁሉ የትኛውም የውጭ ውበት የውስጡን ሰውን አያ...
-
ሰው በእግዚአብሄር አምሳል ተፈጥሮአል፡፡ ሰው ለእግዚአብሄር ክብር ተፈጥሯል፡፡ ሰው የተፈጠረበትን አላማ አግኝቶ ካልፈፀመው ህይወቱን ያባክናል፡፡ ሰው እግዚአብሄር ለእርሱ ያለውን አላማ አግኝቶ ከፈፀመው ግን በህይወት ...
-
በነጻነት ሕግ ፍርድን ይቀበሉ ዘንድ እንዳላቸው ሰዎች እንዲህ ተናገሩ፥ እንዲህም አድርጉ። የያዕቆብ መልእክት 2፡ 12 በክርስቶስ ከሃጢያት እስራትና ፍርድ ነፃ ወጥተናል፡፡ ነገር ግን ነፃነት የሚመጣ...
Monday, September 9, 2019
ምሕረቱ ለዘላለም ነውና
Subscribe to:
Post Comments (Atom)

No comments:
Post a Comment