|
መዝሙረ
ዳዊት 136
|
||
|
እግዚአብሔርን
አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
የአማልክትን
አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
የጌቶችን
ጌታ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
እርሱ
ብቻውን ታላቅ ተኣምራትን ያደረገ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ሰማያትን
በብልሃት የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ምድርን
በውኃ ላይ ያጸና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ብቻውን
ታላላቅ ብርሃናትን የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ለፀሐይ
ቀንን ያስገዛው፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ለጨረቃና
ለከዋክብትም ሌሊትን ያስገዛቸው፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ከበኵራቸው
ጋር ግብጽን የመታ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
እስራኤልንም
ከመካከላቸው ያወጣ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
በጸናች
እጅ በተዘረጋችም ክንድ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
የኤርትራን
ባሕር በየክፍሉ የከፈለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
እስራኤልን
በመካከሉ ያሳለፈ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ፈርዖንንና
ሠራዊቱን በኤርትራ ባሕር የጣለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ሕዝቡን
በምድረ በዳ የመራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ታላላቅ
ነገሥታትን የመታ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ብርቱዎችንም
ነገሥታት የገደለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
የአሞራውያንን
ንጉሥ ሴዎንን፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
የባሳንን
ንጉሥ ዐግን፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ምድራቸውን
ርስት አድርጎ የሰጠ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ለባሪያው
ለእስራኤል ርስት፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
እኛን
በመዋረዳችን አስቦናልና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ከጠላቶቻችንም
እጅ አድኖናልና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና
|
||
|
ለሥጋ
ሁሉ ምግብን የሚሰጥ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
የሰማይን
አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ብዙ ጊዜ አመት ሲጠቀስ አብሮ ዓ.ም. ወይም አመተ ምህረት ተብሎ ይጠቀሳል፡፡ ይህ አመተ ምህረት የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ ሊሰቀል ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ያለውን ጊዜ ነው...
-
ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። 2 ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5 ፡ 17 የሰውን ማንነቱን ፣ ተፈጥሮውን ፣ ባህ...
-
ጸሎት ከእግዚአብሄር ጋር መነጋገር ነው። ጸሎት ሊደረግ የሚችለው ከእግዚአብሄር ጋር በመግባባት ብቻ ነው። ጸሎት የሚሰምረው እንደ እግዚአብሄር አሳብ ስንጸልይ ብቻ ነው። በአጠቃላይ ለእግዚአብሄር ያለን አመለካከት ...
-
We are created to be free moral beings. Man thinks before he decided to do something. He only does what he decided to do. For as he ...
-
ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ። ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለ...
-
ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም፤ ትንቢት ቢሆን ግን ይሻራል፤ ልሳኖች ቢሆኑ ይቀራሉ፤ እውቀትም ቢሆን ይሻራል። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡8 ፍቅር ዘላለማዊ ነው፡፡ ፍቅር የእግዚአብሄር ባህ...
-
በእነዚህ ቀናት ከእግዚአብሄር ውጭ ለሰው ለመላእክት ለቅዱሳን ለሰማእታት ስግደት ይገባል አይገባም ስግደት ከተገባስ እስከምን ድረስ ነው ስግደት የሚገባው የሚለው ጥያቄ ሲያከራክር ቆይቶዋል፡፡ የዚህ ፅሁፍ አላማ የስ...
-
የምንሞትለት እንጂ የምንገድልለት አምላክም ሆነ ሀይማኖት የለንም! አምላክ ሀያል ነው የእኛ እርዳታ አይፈልግም። እንዲገድሉለት የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት እውነተኛ ሀይማኖት አይደለም። የሰውን እርዳታ የሚፈልግ...
Monday, September 9, 2019
ምሕረቱ ለዘላለም ነውና
Subscribe to:
Post Comments (Atom)

No comments:
Post a Comment