|
መዝሙረ
ዳዊት 136
|
||
|
እግዚአብሔርን
አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
የአማልክትን
አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
የጌቶችን
ጌታ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
እርሱ
ብቻውን ታላቅ ተኣምራትን ያደረገ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ሰማያትን
በብልሃት የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ምድርን
በውኃ ላይ ያጸና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ብቻውን
ታላላቅ ብርሃናትን የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ለፀሐይ
ቀንን ያስገዛው፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ለጨረቃና
ለከዋክብትም ሌሊትን ያስገዛቸው፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ከበኵራቸው
ጋር ግብጽን የመታ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
እስራኤልንም
ከመካከላቸው ያወጣ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
በጸናች
እጅ በተዘረጋችም ክንድ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
የኤርትራን
ባሕር በየክፍሉ የከፈለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
እስራኤልን
በመካከሉ ያሳለፈ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ፈርዖንንና
ሠራዊቱን በኤርትራ ባሕር የጣለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ሕዝቡን
በምድረ በዳ የመራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ታላላቅ
ነገሥታትን የመታ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ብርቱዎችንም
ነገሥታት የገደለ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
የአሞራውያንን
ንጉሥ ሴዎንን፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
የባሳንን
ንጉሥ ዐግን፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ምድራቸውን
ርስት አድርጎ የሰጠ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ለባሪያው
ለእስራኤል ርስት፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
እኛን
በመዋረዳችን አስቦናልና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
|
||
|
ከጠላቶቻችንም
እጅ አድኖናልና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና
|
||
|
ለሥጋ
ሁሉ ምግብን የሚሰጥ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
|
የሰማይን
አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
|
||
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
Name it claim it Take it! “So Jesus answered and said to them, “Have faith in God. For assuredly, I say to you, whoever says to this mount...
-
We are created to be free moral beings. Man thinks before he decided to do something. He only does what he decided to do. For as he ...
-
ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና። 1ኛ ዮሐንስ 4፡4 አለም በክፉ ተይዞዋል፡፡ አለም እንዲደግፈንና እንዲያበረታታን አንጠብቅም፡፡ አ...
-
ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ማቴዎስ 5፡10 አለም በክፉ ተይዞአል፡፡ ሰው እግዚአብሄርን ሲያመልክና ሲከተል ከብዙ ሰዎች መካከል ተለይቶ ይወጣል፡፡ በክርስትና ለጌታ ብ...
-
“ አስቀድማችሁ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ፥ እርሱም ግብዝነት ነው። ” የሉቃስ ወንጌል 12 ፡ 1 የፈሪሳዊያን ትምህርት ተጠበቁ ሲባል አንድን የህብረተሰብ ክፍል ወይም አንድን ሃይማኖት የሚመለከት በፍ...
-
እግዚአብሄርን ማገልገል የሚችለው ባለው ነገር የሚረካ ሰው ብቻ ነው በህይወት የምንፈልገው ገደብ የለሽ ነው። የሆነ ነገር እንዲኖርህ ትመኛለህ እና ልክ ስታገኘው በፊትህ ክብሩን ያጣል። አንድን የተሻለን ነገር የሚፈልጉ ሰ...
-
የዲያቢሎስ አላማ አንድና አንድ ነው፡፡ ዲያቢሎስ ከመጣ ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ለሌላ ነገር አይመጣም፡፡ ዲያቢሎስንብ የመጋዣው መንገድ ደግሞ በእግዚአብሄር ላይ ማመፅ ወደ እግዚአብሄር...
Monday, September 9, 2019
ምሕረቱ ለዘላለም ነውና
Subscribe to:
Post Comments (Atom)

No comments:
Post a Comment