Popular Posts

Monday, September 2, 2019

የምስራች በእግዚአብሄር የተመረጠ ሞኝ ደካማ ምናምንቴ የተናቀ ያልሆነ



እግዚአብሄር አላማውን ለመፈፀም በማንም ሰው ላይ አይደገፍም፡፡ እግዚአብሄር ለመስራት ጥበበኛን አይፈልግም፡፡ ጥበበኛውን ለማሳፈር እግዚአብሄር በእግዚአብሄር ፊት ሞኝ የሆነውን ሰው ይጠቀማል፡፡
ከእናንተ ማንም በዚች ዓለም ጥበበኛ የሆነ ቢመስለው ጥበበኛ ይሆን ዘንድ ሞኝ ይሁን። የዚህች ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና። እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ፤ ደግሞም፦ ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ከንቱ እንደ ሆነ ያውቃል ተብሎ ተጽፎአልና። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 3፡18-20
እግዚአብሄር ሊጠቀምብን መሰጠትን ብቻ እንጂ ሌላ ምንም መመዘኛ አልጠበቀብንም፡፡
ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁን ተመልከቱ፤ እንደ ሰው ጥበብ ጥበበኞች የሆኑ ብዙዎች፥ ኀያላን የሆኑ ብዙዎች፥ ባላባቶች የሆኑ ብዙዎች አልተጠሩም። ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን እንዲያሳፍር የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ፤ ብርቱንም ነገር እንዲያሳፍር እግዚአብሔር የዓለምን ደካማ ነገር መረጠ፤ እግዚአብሔርም የሆነውን ነገር እንዲያጠፋ የዓለምን ምናምንቴ ነገር የተናቀውንም ነገር ያልሆነውንም ነገር መረጠ፥ 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፡26-28
ብዙ ጊዜ ሰው በሃይሉ የሚበረታ እና እግዚአብሄር እንደማያስፈልገው ያስባል፡፡ ነገር ግን ሰው በሃይሉ አይበረታም፡፡ የሰው ሃይል ምንም አያመጣም፡፡
እግዚአብሄር ለመርዳት የማንንም እርዳታ አይጠይቅም፡፡
ከሕዝቡ መኳንንት ጋር ያስቀምጣቸው ዘንድ፥ የክብርንም ዙፋን ያወርሳቸው ዘንድ፥ ችግረኛውን ከመሬት ያስነሣል፥ ምስኪኑንም ከጉድፍ ያስነሣል፤ የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና፥ በእነርሱ ላይም ዓለምን አደረገ። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 2፡8
እግዚአብሄር አቤት እርሱ ተብሎ በተደነቀለት በብዙ ሃያል ዝነኛና ጥበበኛ ከማዳን ይልቅ በጥቂት ማዳንን ይመርጣል፡፡ በብዙ ወይም በጥቂት ማዳን እግዚአብሔርን አያስቸግረውም፡፡
ዮናታንም ጋሻ ጃግሬውን፦ ና፥ ወደ እነዚህ ቈላፋን ጭፍራ እንለፍ፤ በብዙ ወይም በጥቂት ማዳን እግዚአብሔርን አያስቸግረውምና ምናልባት እግዚአብሔር ይሠራልን ይሆናል አለው። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 14፡6
እርሱ ብቻውን ታላቅ ተኣምራትን ያደረገ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ መዝሙረ ዳዊት 1364
በሃይሉ እንደማይበረታ የሚያስተውል ሰው ሲያገኝ እግዚአብሄር ሃይሉን ይገልጥበታል፡፡
እግዚአብሔር ልቡ በእርሱ ዘንድ ፍጹም የሆነውን ያጸና ዘንድ ዓይኖቹ በምድር ሁሉ ይመለከታሉና። መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 16፡9
የህይወት ቁልፍ ያለው እግዚአብሄር ጋር እንጂ ሃያል ጥበበኛና ባለጠጋ ጋር እንዳልሆነ የሚያስተውል ደካማ ሰው ሲያገኝ እእግዚአብሄር ለታላላቅ ነገር ይጠቀምበታል፡፡ እግዚአብሄር ህይወታችን ሊለውጥ ሃይላችንን ጥበባችንና ብልጥግናችንን አይፈልግም፡፡ እግዚአብሄር ሃይል ፣ ጥበብና ብልጥግና የሌላቸውን ደካማ ሰዎች ህይወት በመለወጥ የተካነ ነው፡፡
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው፦ ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ትንቢተ ኤርምያስ 9፡23-24
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ጥበብ #ማስተዋል #ሞኝ #ደካማ #ምናምንቴ #የተናቀ #ያልሆነ #መረዳት #ሃያል #ጠቢብ #ባለጠጋ #ውርደቱ #ይመካ #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #መመካት #ብርታት #እምነት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ 

No comments:

Post a Comment