Popular Posts

Saturday, September 28, 2019

ይቅርታ አንጠይቅም




ስለአፈጣጠራችን ማንምም ሰው ይቅርታ አንጠይቅም፡፡
እግዚአብሄር አንድ ቀን ተገልጦ እኛን እንደዚህ አድርጌ ስለፈጠርኳቸው ይቅርታ እጠይቃለሁ ሲል አታገኙትም፡፡ እግዚአብሄር እንደዚህ አድርጎ ስለፈጠረን አይፀፀትም፡፡ እግዚአብሄር ስለአፈጣጠራችን ማንንም ይቅርታ አይጠይቅም፡፡ እግዚአብሄር ስለፈጠረን ስለባህሪያችን ፣ ስለመልካችን ፣ ስለዘራችን ስለአገራችን ማንንም ይቅርታ አይጠይቅም፡፡ እግዚአብሄር ግሩምና ድንቅ አድርጎ ፈጥሮናል፡፡
ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ፤ ሥራህ ድንቅ ነው፥ ነፍሴም እጅግ ታውቀዋለች። መዝሙረ ዳዊት 139፡14
ሰው ሲያየን እንዲህ ተደርገው ቢፈጠሩ ኖሮ መልካም ነበር ብለው አፈጣጠራችንን ለማስተካከል ሊፈተኑ ይችላሉ፡፡ ሰው አንዳንድ ጊዜ ነሸጥ ሲያደርገው እግዚአብሄርን ሊያርም ይዳዳዋል፡፡ ሰው የእግዚአብሄርን ፍጥረት ለማስተካል መፈተኑ የእርሱ ችግር እንጂ የእግዚአብሄር ወይም የተፈጠረው ሰው ችግር አይደለም፡፡
ስለደረስንበት መንፈሳዊ ደረጃ ማንንም ይቅርታ አንጠይቅም
አንዳንድ ጊዜ ሰይጣን ከሚያመጣብን ኩነኔ ተነስተን ያለንበትን መንፈሳዊ ደረጃ መቀበል ያቅተናል፡፡ ስለዚህ ስለመንፈሳዊ የህይወት ደረጃችን እንሳቀቃለን፡፡ ስለደረስንበት መንፈሳዊ ደረጃችን እናዝናለን እንኮነናለን ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡ ስለደረስንበት መንፈሳዊ ደረጃ ማነስ ስለምንሳቀቅ ከደረስንበትን መንፈሳዊ ደረጃ በላይ እንደደረስን ለሌሎች ለማሳየት እንፈተናለን፡፡ የደረስንበትን መንፈሳዊ ደረጃ አጋንነን መናገር መፈለጋችን ስላለንበት መንፈሳዊ ደረጃ ደስተኞች አለመሆናችንን ያመለክታል፡፡ ስለደረስንበት መንፈሳዊ ደረጃ ምቾት ስለማይሰማን መድረስ ይገባን ነበር ብለን ስለምናስበው መንፈሳዊ ደረጃ ሰዎችን ሃገርን ራሳችንን እንኮንናለን፡፡   
እውነት ነው ልደርስበት ካለው መንፈሳዊ ደረጃ እንፃር ያለንበት መንፈሳዊ ደረጃ ያነሰ ነገር ነው፡፡ ነገር ግን ያለንበት መንፈሳዊ ደረጃ ከነበርንበት መንፈሳዊ ደረጃ እንፃር ደግሞ ህልምን በእውን እንደመኖር በብዙ እጅ የተሻለ ነው፡፡ ያለሁንበት መንፈሳዊ ደረጃ ወደፊት መድረስ ካለብን መንፈሳዊ  ደረጃ ቢያንስም ከነበርንበት መንፈሳዊ ደረጃ ቢበልጥም ላለንበት ጊዜ ፍፁም ነው፡፡
ነገር ግን በእናንተ ዘንድ ወይም በሌላ ሰው ዘንድ ብፈረድ ለእኔ ምንም አይደለም፤ እኔም በራሴ እንኳ አልፈርድም፤ 1 ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 43
ስለደረስንበት የገንዘብ ሁኔታ ማንንም ይቅርታ አንጠይቅም
አንዳንድ ጊዜ ራሳችንን ካለአግባብ ከሌሎች ጋር በማስተያየት እና በማወዳር በስራ አለም ይሄን ያህል ቆይቼ በማለት ምን አለኝ ብለን ራሳችንን እንኮንናለን፡፡ ራሳችንን ከሌሎች ጋር ካስተያየን ያለንበትን የገንዘብ ሁኔታ ለመቀበል ይቸግረናል፡፡ ስለዚህ ከአቅማችን በላይ ውድ ነገሮችን በመግዛት ካለን ገንዘብ በላይ እንዳለን ለሌሎች ለማሳየት እንፈተናለን፡፡ እግዚአብሄር ያለንበትን የገንዘን ሁኔታ አበጥሮ ያውቃል፡፡ የገንዘብ ሁኔታችንን በተመለከተ እግዚአብሄር ከየት እንደመጣን ፣ አሁን የት እንደደረስንና ወደየት እየሄድን እንዳለን ያውቃል፡፡ እግዚአብሄር ስለእኛ የገንዘብ ሁኔታ አይሳቀቅም፡፡ እግዚአብሄር እኛ ስላለንበት የገንዘብ ሁኔታ ማንንም ይቅርታ አይጠይቅም፡፡
እኛም ስላለንበት የገንዘብ ሁኔታ ምንንም ይቅርታ መጠየቅ የለብንም፡፡ እግዚአብሄር ስላደረሰን የገንዘብ ሁኔታ እርማት እና ማስተካያ ሊሰጥ የሚፈተን ሰው ካለ ያ የእርሱ ችግር እንጂ የእኛ ችግር አይደለም፡፡  
ስለሌለን ስጦታ ማንንም ይቅርታ አንጠይቅም፡፡
ወደምድር ስንፈጠረ ሁላችንም ለምድር ከሚጠቅም ስጦታ ጋር ተፈጥረናል፡፡ ማን ከምን ስጦታ ጋር እንደሚፈጠር የሚወስነው እኛ ሳንሆን እግዚአብሄር ራሱ ነው፡፡ ሌሎች በጣም ስልተካኑት እኛ ግን ስለሌለን ስጦታ ማንም እንዲኮንነን አንፈቅድለትም፡፡
በክርስትናም መንፈስ ቅዱስ እንደወደደ ስጦታዎችን ያካፍላል፡፡ ስጦታን የሚሰጠው እግዚአብሄር እንጂ እኛ ስላይደለን ስለሌለን መንፈሳዊ ስጦታ ማንንም ይቅርታ መጠየቅ የለብን፡፡
እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም። ወደ ሮሜ ሰዎች 8፡1
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa37/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ግሩም #ድንቅ #ክርስቶስ #ህይወት #ብልፅግና #የብልፅግናወንጌል #መፀለይ #ሞገስ #በረከት #ስኬት #እረኛእግዚአብሄር #ስምረት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #የተትረፈረፈህይወት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መርካት #ደስታ #እረፍት

No comments:

Post a Comment