Popular Posts

Sunday, September 1, 2019

ስኬት ውስጤ ነው



እግዚአብሄር በሁሉም አቅጣጫ ስኬታማ ነው፡፡ ሰውን የፈጠረው እግዚአብሄር ነው፡፡ እግዚአብሄር ደግሞ ስስታም አይደለም፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ቁርጥ እርሱን አስመስሎ በመልኩና በአምሳሉ ነው፡፡
እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ እንዲህም አላቸው፦ ብዙ፥ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት፥ ግዙአትም፤ የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ግዙአቸው። ኦሪት ዘፍጥረት 1፡27-28
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው እንደእርሱ ሙሉ ለሙሉ ስኬታማ እንዲሆን ነው፡፡
እግዚአብሄር ሰውን ሲፈጥረው ለስኬት የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ በውስጡ አስቀምጦ ነው፡፡
ሰው ለስኬቱ የሚያስፈልገው ነገር ሁሉ በውስጡ አለ፡፡ የሰው ስኬት በሌላ ሰው በጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተ አይደለም፡፡ ሌላው ሰው እንዲሳካልን ቢፈልግም ባይፈልግም ለስኬት የሚያስፈልገው ነገር በውስህ አለ፡፡ ስኬት በገንዘብ ወስጥ የለም ስኬት በዝና ውስጥ የለም ስኬት በሃይል ውስጥ የለም፡፡ ስኬት ያለው በአንተ ውስጥ ነው፡፡ ስኬት በውስጥህ ስላለ እና ለስኬታማነት ስለተቀረፅክ እና ስለተነደፍክ ገንዘብ ፣ ዝና እና ስልጣን በሌለበት ቦታ ብትጣል ይሳካልሃል፡፡ የሚያሳካለህ እግዚአብሄር ከአንተ ጋር መኖሩ ብቻ ነው፡፡
በሕይወትህ ዕድሜ ሁሉ ማንም አይቋቋምህም፤ ከሙሴ ጋር እንደ ሆንሁ እንዲሁ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ አልጥልህም፥ አልተውህም። መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 1፡5
ሁኔታዎች አይሳካልህም ቢሉም ለስኬት ከሚያስፈልገው ማንኛውም ነገር ጋር ተፈጥረናል፡፡ ሊሳካልህ አይችልም ብሎ ያሳመነህ ካለህ ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ ብቻ የሚመጣው የሰይጣን ድምፅ ብቻ ነው፡፡
ሰው በውስጡ ያለውን የስኬት ንጥረ ነገር በታማኝነት ካወጣው እና ከሰራበት ስኬትን የሚወስድበት ማንም የለም፡፡ ሰው በውስጡ ያለውን የስኬት ንጥረ ነገር በትጋት ከሰራበት ሰይጣነም ሆነ ሰው ከስኬት ሊያቆመው አይችልም፡፡
ሰው እንኳን ለመኖር የሚያስፈልገው ይቅርና ሌሎችን ሊያገለግልበትና ሊባርክበት የሚችልበት ትልቅ የተጠራቀመ ጉልበት በውስጡ አለ፡፡ እንዲያውም ሰው የተፈጠረው ለራሱ እንዲሳካለት አይደለም፡፡ ሰው የሚሳካለት እግረመንገዱን በነው፡፡ ሰው የተፈጠረው ከራሱ አልፎ ሌሎችን ለስኬት ለመርዳት ነው፡፡
የስኬታማ ሰዎችና ያልተሳካለቻው ሰዎች የሚለዩት በውስጣቸው ባለው የስኬት ዘር ሳይሆን የስኬት ዘሩን አውጥተው በመጠቀማቸውና ባለመጠቀማቸው ብቻ ነው፡፡ አንዳንዱ እዲሳካለትና አንዳንዱ እንዳይሳካለት ታቅዶ አልተፈጠረም፡፡ ህሊናውን ጠብቆ የሚኖር ሰው ሁሉ እንዲሳካለት ለስኬት ከሚያስፈልገው ነገር ሁሉ ጋር ተፈጥሮአል፡፡
የሰው ስኬት የሚለካው በጎረቤቱ የስኬት መመዘኛ አይደለም፡፡ የሰው ስኬት የሚለካው በልቡ በተቀመጠው ክህሎት ነው፡፡ ምንም ከሌሎች የተለየ ቢሆን በልቡ የተቀመጠውን የስኬት ዘር አውጥቶ ከዘራው ፣ ከኮተኮተውና ከተንከባከበው ሰው ሁሉ በራሱ መንገድ ስኬታማ መሆን ይችላል፡፡
ሰው አግዚአብሄር ለምን እንደፈጠረው እግዚአብሄር የፈጠረበትን አላማ ከእግዚአብሄር ቃል ፈልጎ ካገኘውና የህይወት አላማ እና እቅድ  በትጋት ከተከተለ የማይሳካለት ምንም ምክኒያት የለም፡፡
አንተ ስኬትን ከምትፈልገው በላይ እግዚአብሄር እንዲሳካልህ ይፈልጋል፡፡ እንዲሳካልህ መፈለግና ውድቀትን መጥላትን በውስጥህ ያስቀመጠው በነገር ሁሉ እንዲከናወንልህ የሚፈልገው እግዚአብሄር ራሱ ነው፡፡
ወዳጅ ሆይ፥ ነፍስህ እንደሚከናወን፥ በነገር ሁሉ እንዲከናወንልህና ጤና እንዲኖርህ እጸልያለሁ። 3ኛ የዮሐንስ መልእክት 1፡2
እንዲሳካልህ የሚያስፈልገውን ቁልፍ ነገር በየጊዜው የሚያስታውስህ እንዲሳካልህ የእግዚአብሄር በጎ ፈቃድ ስለሆነ ነው፡፡
በምትሄድበትም ሁሉ እንዲከናወንልህ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አትበል። የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም። መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 1፡7-8
የስኬትን መንገድ የሚያስተምርህ እውነተኛ ስኬት እንዲኖርህ የሚያስፈልገውን ሁሉ ስለሰጠህና ለስኬትህ አብሮ መስራት ስለሚፈልግ ነው፡፡
ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ። ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል። መዝሙረ ዳዊት 1፡1-3
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ስኬት #ብልፅግና #የብልፅግናወንጌል #ደስታ #እርካታ #ሰላም #ምሪት #ፍቅር #እምነት #መፀለይ #ሞገስ #በረከት #ስኬት #እረኛእግዚአብሄር #ስምረት #መሰረታዊፍላጎት #ሁሉየእናንተነውና #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #የተትረፈረፈህይወት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መርካት #ደስታ #የልብስፋት #ማስተዳደር #እረፍት

No comments:

Post a Comment