Popular Posts

Tuesday, September 24, 2019

የምታስበው ክፉ ሀሳብ ይታያል



ብዙ ሰው የሚያስበው አሳብ በሌላ ሰው እንደሚታይ አያስብም:: እግዚአብሄር ወደአእምሮህ የመጣውን አሳብ በአጭሩ የቀጨኸውን ሃሳብ ያስተናገድከውንና በውስጥህ የበቀለውን እና ፍሬ ያፈራውን አሳብ ሁሉ ያያል ያውቃል፡፡
መልካም ብታደርግ ፊትህ የሚበራ አይደለምን? መልካም ባታደርግ ግን ኃጢአት በደጅ ታደባለች፤ ፈቃድዋም ወደ አንተ ነው፥ አንተ ግን በእርስዋ ንገሥባት። ኦሪት ዘፍጥረት 4፡7
ብዙ ሰው የሚያስበው አሳብ በሌላ ሰው እንደሚታይ አድርጎ አይጠነቀቅም:: ብዙ ሰው ሃሳቡ እንደማይታይ አድርጎ ስለሚኖር ብዙ ጊዜ ችግር ውስጥ ይገባል::
ሰው የሚኖረው ያሰበውን አሳብ ነው፡፡ ሰው የሚተገብረው ያሰበውን አሳብ ነው፡፡
በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና፤ መጽሐፈ ምሳሌ 23፡7
ያሰብነውን ስለምንኖረው በእኛ ውስጥ ያስተናገድነው አሳብ ሁሉ ይታያል::
እውነት ነው ወደአእምሮዋችን የሚመጣ ሃሳብ ሁሉ አይታይም:: ነገር ግን የምናስተናግደው ሃሳብ ይፍጠንም ይዘግይም ይታያል:: ወደ አእምሮዋችን ሲመጣ እንደቆሻሻ ቆጥረን እሽቀንጥረን ከአእምሮዋችን የማናስወጣው ክፉ ሃሳብ በሰው ዘንድ ይታያል ያዋርደናል::
ወደአእምሮዋችን የሚመጣውን የንቀት ሃሳብ በፍጥነት በእንጭጩ ካልቀጭነው ወደድንም ጠላንም በዝንባሌያችንንና በአመለካከታችን ይንፀባረቃል:: ስለሌላው ሰው የንቀት ሃሳብ ሲመጣልን ደስ ከተሰኘንበት ካስተናገድነውና ካሰላሰልነው በአመለካከታችን ይንፀባረቃልሸ  
አንዳንድ ሰዎች ስለክፉ ንግግራቸው ስለዝንባሌና አመለካከታቸው መነሻ ችግር ከስር መሰረቱ መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ ከንፈራቸው ላይ ሊያስተካክሉ ይፈልጋሉ::
ችግሩ ክፉ ሃሳብ በንግግርም ባይታይ በአመለካከት ይታያል:: ክፉ ሃሳብ በአመለካከት ባይታይም በንግግር ይታያል፡፡
የአፍ ወለምታ በቅቤ አይታሽም ይባላል:: እውነት ነው የንግግር ስህተት አይስተካከልም:: የአፍ ወለምታ የአስተሳሰብ ወለምታ ማሳያው ነው:: ንግግር የአስተሳሰብ መስታወት ነው:: ዛፍ የሚቃናው በችግኝነት ደረጃ እንደሆነ ሁሉ ንግግር የሚስተካከለው በሃሳብ ደረጃ  ብቻ ነው::
ሃሳባችንን እንደፈለግን ለቀነው በእግዚአብሄር እውቀት ላየ የሚነሳውን የሰውን ሃሳብ ካላዋረድነው ሃሳብ ይታያል፡፡
የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፥ 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10፡5
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ትህትና #መዋረድ #ባህሪ #ዝቅታ #ትዕቢት #ትምክህት #መመካት #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አመለካከት #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment