Popular Posts

Friday, August 30, 2019

የፍሬ ፍሬ


ለፍሬያማነት መተከልና ስር መስደድ ወሳኝ ነው፡፡ የትኛውም ዘር ስር ሳይሰድ ፍሬ ሊያፈራ አይችልም፡፡ ዘር ፍሬ ለማፍራት መጀመሪያ ከምንጩ ጋር መገናኘት ይኖርበታል፡፡ ዘር አድጎ ፍሬ ከማፍራቱ በፊት ፍሬ ሊያፈራ ከሚያስችለው አቅራቦት ጋር በሚገባ መገናኘት አይችልም፡፡
እድገቱ አስተማማኝ እንዲሆን ተክል ስር መስደድ አለበት፡፡ ተክል እንዲያድግና እንዲፈራ ክር መስደድ ወሳኝ ነው፡፡ አንድ ተክል ሊያድግና ፍሬ ሊያፈራ የሚችለውስር በሰደደው መጠን ብቻ ነው፡፡
በክርስትናም ለማደግና ፍሬ ለማፍራት ለማደግ ከሚያስፈልገው ከእግዚአብሄር ቃል ጋር በሚገባ መገናኘት ይጠይቃል፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ሳይዙ ለማደግ እና በህይወት ፍሬ ለማፍራተ መሞከር መሰረት ሳይሰሩ ቤት ለመስራት እንደመሞከር ከንቱ ድካም ነው፡፡
ይህንም ቃሌን ሰምቶ የማያደርገው ሰው ሁሉ ቤቱን በአሸዋ ላይ የሠራ ሰነፍ ሰውን ይመስላል። ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት መታው፥ ወደቀም፥ አወዳደቁም ታላቅ ሆነ። የማቴዎስ ወንጌል 7፡26-27
ስር ካልሰደደ ተክል እድገትና ፍያማነት መጠበቅ ከንቱ እንደሆነው ሁሉ በእግዚአብሄር ቃል ልምምድ ስር ካልሰደደ ክርስትያን መንፈሳዊ እድገትና ፍሬያማነት መጠበቅ ሞኝነት ነው፡፡  
ሥር ሰዳችሁ በእርሱ ታነጹ፥ እንደ ተማራችሁም በሃይማኖት ጽኑ፥ ምስጋናም ይብዛላችሁ። ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2፥7
ስርና መሰረታቸው በእግዚአብሄር ቃል በጌታ ያልፀኑ ሰዎች የማይያዙ የማይጨበጡ በጠንካራ መሰረት ላይ ያልታነፁ ሰዎች ናቸው፡፡  
እንደ ስሕተት ሽንገላ ባለ ተንኮል በሰዎችም ማታለል ምክንያት በትምህርት ነፋስ ሁሉ እየተፍገመገምን ወዲያና ወዲህም እየተንሳፈፍን ሕፃናት መሆን ወደ ፊት አይገባንም፥ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4፡14
በአንዴ የሚያፈራ ተክል እንደሌለ ሁሉ ለማፍራት መቆየት እና መኖር ይጠይቃል፡፡ ለማፍራት ራስን በመስጠት መጠበቅ ይጠይቃል፡፡ ለማፍራት ራስን በመስጠት መቆየት መኖር ይጠይቃል፡ 
በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ። ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ባይኖር ከራሱ ፍሬ ሊያፈራ እንዳይቻለው፥ እንዲሁ እናንተ ደግሞ በእኔ ባትኖሩ አትችሉም። የዮሐንስ ወንጌል 15፡4
በመልካም መሬት ላይም የወደቀ እነርሱ በመልካምና በበጎ ልብ ቃሉን ሰምተው የሚጠብቁት በመጽናትም ፍሬ የሚያፈሩ ናቸው። የሉቃስ ወንጌል 8፡15
ምንም ግንኙነት ካለመቆየት ፍሬ አይሰጥም፡፡ የተክሉና ለተክሉ የሚያስፈልገው ነገር ሁሉ በስሩ አማካኝነት ካልተገናኘ ተክሉ ፍሬ ሊያፈራ አይችልም፡፡ በየጊዜው አዳዲስ ቦታ የሚተከል ችግኝ መጠውለጉና ለፍሬ ሳይበቃ መድረቁ አይርም፡፡  
በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታችሁ በኃይል እንድትጠነክሩ ክርስቶስም በልባችሁ በእምነት እንዲኖር እንደ ክብሩ ባለ ጠግነት መጠን ይስጣችሁ፤ የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ፥ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 3፥16-17
እግዚአብሄርን የምናስከብረው በፍሬ ብቻ ነው፡፡
በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል። ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከበራል። የዮሐንስ ወንጌል 157-8
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ሬያማነት #ፍሬ #ስር #መሰረት #ማፍራት #ስኬት #በእኔኑሩ #ቃል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መመዘኛ #መስፈርት #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment