Popular Posts

Saturday, March 23, 2019

አውቆ ነው

በህይወት በሰዎች በደል አለመሰናከልን የመሰለ ታላቅ ችሎታ የለም፡፡ ተበድሎም ማለፍን የመሰለ ነፃነት የለም፡፡ ሰው የሚያቆስል ንግግር ሲናገርህ ሰምተህ እንዳልሰማህ ማለፍና ህይወትህን መቀጠል ሀብት ነው፡፡  የናቀህን መልሰህ ለመናቅ የሚፈትንህን ፈተና በትግስት ማለፍና የናቀህን አለመናቅን የመሰለ በረከት የለም፡፡
ይቅር አለማለት የአንዳንድ ሰዎችን እምቅ ጉልበት በመብላት ህይወታቸውን ሽባ አድርጓል፡፡ በደልን አለመተው የአንዳንድ ሰውን ሩጫ ገቷል፡፡ በደልን መቁጠር ብዙ ሰዎችን ጠላልፎ ከህይወት መንገድ ጥሏል፡፡  
ይቅር አለማለት ጉልበትን ላልታለመለት አላማ በከንቱ ማባከን ነው፡፡
እግዚአብሄር ለእኛ ነው እግዚአብሔር በክፉ አይፈትነንም፡፡
እንዲያውም ከምንችለው በላይ እንድንፈተን አይፈቅድም፡፡ የበደለን ይቅር ማለት እንደምንችል ያውቃል፡፡ በህይወታችን ያለፈው ፈተና ሁሉ ያለፈው ፈተናውን ሁሉ ልናልፈው እንደምንችል እግዚአበሄር አውቆ ነው፡፡
ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10፡13
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪ #ፀጋ #የሚያስችልሃይል #የሚረዳንን #ፀሎት #እውቀት #ምስጋና #ትህትና #ልብ #እምነት #ፀሎት #ማማጠን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment