Popular Posts

Monday, March 11, 2019

ስድብን በስድብ


ከልብ ክፉ አሳብ፥ መግደል፥ ምንዝርነት፥ ዝሙት፥ መስረቅ፥ በውሸት መመስከር፥ ስድብ ይወጣልና። የማቴዎስ ወንጌል 1519
አሁን ግን እናንተ ደግሞ ቍጣንና ንዴትን ክፋትንም፥ ከአፋችሁም ስድብን የሚያሳፍርንም ንግግር እነዚህን ሁሉ አስወግዱ፤ ወደ ቆላስይስ ሰዎች 38
ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና። 1 የጴጥሮስ መልእክት 39
ስድብ ከስጋ የሃጢያት ስራዎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ስድብ በንግግር ሌላውን ዝቅ ዝቅ ማድረግ ነው፡፡ ስድብ በንቀት ንግግር መናገር ነው፡፡ ስድብ ራስን ከፍ ማድረግና ሌላውን ማዋረድ ነው፡፡ ስድብ ሌላውን በማሳነስ የራስን የራስ ወዳድንት ሃሳብ ለማስፈፀም መሞከር ነው፡፡ ስድብ ሌላውን በማጣጣል የራስን ምሰል መገንባት ነው፡፡
ስድብ ከጥላቻ የሚመነጭ የምድር ፥ የሥጋና የአጋንንትም ጥበብ ነው፡፡  
ከእናንተ ጥበበኛና አስተዋይ ማን ነው? በመልካም አንዋዋሩ ስራውን በጥበብ የዋህነት ያሳይ። ነገር ግን መራራ ቅንዓትና አድመኛነት በልባችሁ ቢኖርባችሁ፥ አትመኩ በእውነትም ላይ አትዋሹ። ይህ ጥበብ ከላይ የሚወርድ አይደለም፤ ነገር ግን የምድር ነው፥ የሥጋም ነው፥ የአጋንንትም ነው፤ ቅንዓትና አድመኛነት ባሉበት ስፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ስራ ሁሉ አሉና። የያዕቆብ መልእክት 3፡13-16
ስድብ ሰው ሌላውን በሃሳብ ብልጫ ለማሸነፍ እንደማይችል ተስፋ የቆረጠ የተሸነፈ ሰው ስልት ነው፡፡ ስድብን የሰነፍ መሳሪያ ነው፡፡ ስድብ በአቋራጭ አላማን የማስፈፀሚያ መንገድ ነው፡፡
የሚሳደብ ሰው የሚያሳዝን ሰው ነው፡፡ የሚሳደብ ሰው በጥላቻ እስራት ውስጥ ስላለ ሊታዘንለት የሚገባ ሰው ነው፡፡ የሚሳደብ ሰው ርህራሄ ሊደረግለት የሚገባ ግራ የገባው ሰው ነው፡፡ የሚሳደብ ሰው የበታችነት ስሜቱን በበላይነት ስሜት ሊያካክስ የሚፈልግ ምስኪን ሰው ነው፡፡ የሚሳደብ ስው እውነተኛ የሚለውጥ እና የሚሰራ ሃይልና አቅም ያጠረው ሰው ነው፡፡
በሚሳደብ ሰው ለንቀና አይገባም፡፡ ከሚሳደብ ሰው ጋር በስድብ ፉክክር ውስጥ መግባት የለብንም፡፡ ለተሳዳቢው ማዘንና መራራት እንጂ ሰው የሚሰድበውን ሰው መልሶ ከሰደበ ወደሚሳደበው ሰው ደረጃ ይወርዳል፡፡ የሚሳድብ ሰው ካየን እንድንራራለት እና እንድንፀልይለት እግዚአብሄር እያስታወስን ማለት ነው፡፡ ሰው ሲሳደብ ሁኔታውን በሚገባ መያዝ እንዳቃተው እና ግራ እንደገባው ተረድተን ልናዝንለት ይገባል፡፡ ሰው ሲሳደብ ልንታገሰው መልሰን በመሳደብ ተሳዳቢው ያለው እስራት ውስጥ ላለመግባት ልንጠነቀቅ ይገባል፡፡
ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3፥9
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ባርኩ #ክፉ #መልካም #በረከት #ልትወርሱ #ትህትና #መልካምነት #መከባበር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ብፅእና  #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አንደበት #ከንፈር #ስድብ

No comments:

Post a Comment