Popular Posts

Friday, March 8, 2019

ፍራ


ፍራ እንጂ የትዕቢትን ነገር አታስብ። ወደ ሮሜ ሰዎች 1120
በህይወት የወደቁ ሰዎች ሁሉ ከመውደቃቸው በፊት እኔ አልወድቅም ብለው አስበው ነበር፡፡ በህይወት የወደቁ ሰዎች ሁሉ ከመውደቃቸው በፊት በኩራት አስበው ነበር፡፡ በህይወት የወደቁ ሰዎች ሁሉ ከመውደቃቸው በፊት ይህ ውድቀት በእኔ ላይ አይደርስም ብለው በኩራት አስበው ነበር፡፡ ከመውደቃቸው በፊት ይህን እንዳሰቡ ማረጋገጫው ላለመውደቅ አለመፍራታቸውና ብሎም በመጨረሻም መውደቃቸው ነው፡፡
ሰው መፍራቱን ሲተውና ሃሳቡን በእርጋታ ከመቆጣጠር ይልቅ ሃሳቡን እንደፈለገ ሲለቀው ለውድቀት ይጋለጣል፡፡ ሰው ከመጠን በላይ ሲዝናናና ሃሳቡን መቆጣጠር ሲያቅተው ይስታል፡፡
እንደ ባለ አእምሮ እንዲያስብ እንጂ ማሰብ ከሚገባው አልፎ በትዕቢት እንዳያስብ በመካከላችሁ ላለው ለእያንዳንዱ በተሰጠኝ ጸጋ እናገራለሁ። ወደ ሮሜ ሰዎች 12፡3
ከሰው ውስጥ ፍርሃት ከጠፋና ሰው በትእቢት ካሰበ የጊዜ ጉዳይ ብቻ ነው እንጂ መውደቁ አይቀሬ ነው፡፡
ትዕቢት ጥፋትን፥ ኵሩ መንፈስም ውድቀትን ይቀድማል። መጽሐፈ ምሳሌ 16፡18
እንዳይወድቁ መፍራትና ራስን በትህትና ማዋረድ መልካም ነገር ነው፡፡ ሰው ራሱን ማዋረድ ካልቻለ ሁኔታዎች ያዋርዱታል፡፡ ሰው ክቡር ነው፡፡ ሰውን ሌላ ሰው ሲያዋርደው መልካም አይደለም፡፡ ሰውን ሁኔታ ሲያዋርደው መልካም አይደለም፡፡ የተሻለው ነገር ሰው እንዳይወድቅ መፍራቱና ራሱን ማዋረዱ ነው፡፡
ብልህ ሰው ክፉን አይቶ ይሸሸጋል፤ አላዋቂዎች ግን አልፈው ይጐዳሉ። መጽሐፈ ምሳሌ 22፡3
ፍራ እንጂ የትዕቢትን ነገር አታስብ። ወደ ሮሜ ሰዎች 11፥20  
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ክብር #ትእቢት #ኩራት #እግዚአብሄር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ትህትና #ራስንማዋረድ #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment