Popular Posts

Wednesday, March 27, 2019

እጅግ በጣም አስተማማኝ ቦታ


ሁሉም ሰው በህይወት እጅግ አስተማማኝ ቦታን ይፈልጋል፡፡ እጅግ አስተማማኝ ቦታ ደግሞ የልብ ሁኔታ እንጂ የተለየ ቦታ ፣ ከተማ ወይም አገር አይደለም፡፡ የልባችን ሁኔታ የቆምንበትን ቦታ አደገኛ ወይም አስተማማኝ ያደርገዋል፡፡ የልባችን ትእቢት ህይወታችንን አደጋ ላይ ሲጥለው የልባችን መዋረድና ትህትናችን ደግሞ የህይወታችንን ስኬታማነት አስተማማኝ ያደርገዋል፡፡
በህይወት ብዙ አደገኛ ቦታዎች ቢኖሩም እንደ ትእቢት እጅግ አደገኛ ቦታ የለም፡፡ በህይወት ብዙ አስተማማኝ ቦታአዎች ቢኖሩም እንደትህትና እጅግ በጣም አስተማማኝ ቦታ ግን የለም፡፡ ትእቢተኝነት ህይወታችንን አደጋ ላይ የሚጥል በእሳት እንደመጫወት አደገኛ ሁኔታ ነው፡፡ ራስን ማዋረድ ከማንኛውም ውድቀት የሚጠብቅ እጅግ አስተማማኝ ስፍራ ነው፡፡
ትህትና ስኬትን ሲቀድም ትእቢት ውድቀትን ይቀድማል፡፡  
ትዕቢት ጥፋትን፥ ኵሩ መንፈስም ውድቀትን ይቀድማል። መጽሐፈ ምሳሌ 16፡18
ትእቢት ለእግዚአብሄር ፣ ለራሳችንና ለሌሎች ሰዎች ያለንን አመለካከት ሲያዛባ ትህትና ግን ለእግዚአብሄር ፣ ለራሳችንና ለሌሎች ያለንን አመለካከት ያስተካክላል፡፡
ትእቢት በእኛ ላይ የእግዚአብሄርን ተቃውሞ ሲቀሰቅስ ትህትና የእግዚአብሄርን እርዳታ ያስገኝልናል፡፡ ትህትና አግዚአብሄር ከእኛ ጋር እንዲወግን ሲያደርገው ትእቢት እግዚአብሄር ከእኛ ጋር እንዲቃረነን ፣ የእኛ ተቃራኒ እንሆንና መንገዳችን ላይ እንዲቆም ያደርገዋል፡፡
ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ይላል። የያዕቆብ መልእክት 4፡6
ትህትናችን ለእግዚአብሄር ትክክለኛውን የአምላክነቱን ቦታ ሲሰጠው ትእቢታችን ግን የእግዚአብሄርን የአምላክነቱን እውቅና ይነፍገዋል፡፡
ትህትና የእግዚአብሄርንም አብሮነት ሲያመጣ ትእቢት የእግዚአብሄርን ቁጣ ይቀሰቅሳል፡፡ የልባችን ትህትና እግዚአብሄር ደስ ብሎት የሚያየውና የሚጎበኘው ሰው ሲያደርገን ትእቢት ደግሞ እግዚአብሄር ፊቱን እንዲመልስብን ያደርጋል፡፡
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሰማይ ዙፋኔ ነው፥ ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ የምትሠሩልኝ ቤት ምን ዓይነት ነው? የማርፍበትስ ስፍራ ምንድር ነው? እነዚህን ሁሉ እጄ ሠርታለችና እነዚህ ሁሉ የእኔ ናቸው፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን ወደዚህ ወደ ትሑት፥ መንፈሱም ወደ ተሰበረ፥ በቃሌም ወደሚንቀጠቀጥ ሰው እመለከታለሁ። ትንቢተ ኢሳይያስ 66፡1-2
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ትህትና #መዋረድ #ባህሪ #ዝቅታ #ትዕቢት #ትምክህት #መመካት #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment