Popular Posts

Saturday, March 16, 2019

ታቦቱን መከተል


ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሄር ክብር እግዚአብሄርን ለማክበር ነው፡፡
ሰው የተፈጠረው የፈለገውን ነገር እንዲያደርግ ሳይሆን እግዚአብሄርን እንዲከተል ነው፡፡ ሰው የሚሳካለት እግዚአብሄርን በቅርበት ሲከተል ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄርን የማይከተል ሰው በነገሮች ሊሳካለት ይችላል በእግዚአብሄር ዘንድ ግን አይሳካለትም፡፡
ስለእኛ ከሃጢያት መዳን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሞተና በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ የምናምን ሁላችን የእግዚአብሄር መንፈስ በእኛ ውስጥ ይኖራል፡፡
የእስራኤል ህዝብ ከግብፅ ሲወጣ የእግዚአብሄርን ታቦት ይከተል ነበር፡፡ ታቦቱ ሲቆም ይቆም ነበር ታቦቱ ሲሄድ ደግሞ ይሄድ ነበር፡፡
ሕዝቡን፦ የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦትና ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ፥ ከሰፈራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት። መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 3፡3
እንዲሳካልን ሌላ ማንንም ሰው መከተል የለብንም፡፡ እግዚአብሄር ለእያንዳንዳችን የተለየ የስኬት አላማ አለው፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።ትንቢተ ኤርምያስ 29፡11
በብሉይ ኪዳን እስራኤላዊያን ታቦቱን እንደሚከተሉ ሁሉ አሁንም እኛ በውስጥታችን ያለውን የእግዚአብሄርን መንፈስ በመከተል  ይሳካልናል፡፡
በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና። የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል። ወደ ሮሜ ሰዎች 8፡14፣16
እናንተም ከቅዱሱ ቅባት ተቀብላችኋል፥ ሁሉንም ታውቃላችሁ። እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 2፡20፣27
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ያድርጉ!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መንፈስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #አማላጅ #ታቦት #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ኦርቶዶክስ #ማርያም #ቅዱሳን #ተዋህዶ 

No comments:

Post a Comment