Popular Posts

Thursday, March 14, 2019

ከፀሎት ወደ ምስጋና ካላደረስክ እምነትህ ለውጤት አልደረሰም


በእግዚአብሄር መልክና አምሳል ለተፈጠረ ሰው እምነት በጣም አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ እግዚአብሄር በተፈጥሮአዊ አይን ስለማይታይ ከእግዚአብሄር ጋር የምናደርጋቸው ነገሮች ሁሉ የሚደረጉት በእምነት ነው፡፡ እምነት በተፈጥሮአዊ አይን ማየት የማይታየውንና የማይያዘውን ነገር ማየትና መያዝ ነው፡፡
ከለእምነት ከእግዚአብሄር ጋር ምንም ነገር ማድርግ አይቻለም፡፡ ካለእምንት አግዚአብሄርን ማስደሰት አይቻልም፡፡ ወደ ዕብራውያን 11፡6
ሰው ከእግዚአብሄር እንዲደረግለት በሚፈልገው ነገር ከፀሎት ወደማመስገን ካልተሸጋገረ አላመነም ማለት ነው፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር የሚፈልገው ነገር እንደተደረገለት ማመን አለበት፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር የሚፈልገው ነገር እንደተሰራለት ማወቅ አለበት፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር የሚጠይቀው ነገር እንደተሰጠው መቁጠር አለበት፡፡
ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል። የማርቆስ ወንጌል 11፡24
የእምነት አባታችን አብርሃም የተስፋ ቃሉን ያገኘው አምኖ ማመስገን ሲጀምር ብቻ ነው፡፡
ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። ወደ ሮሜ ሰዎች 4፡20-21
ወደማመስገን ያልደረስንበት ነገር አላመንም ማለት ነው፡፡ እንዳመንን የሚመሰክረው ወሳኙ ነገር ማመስገንና ለእግዚአብሄር ክብር መስጠት መጀመራችን ነው፡፡ ከእግዚአብሄር እንዲደረግልን የፈለግነው ነገር እንዳገኘነው ደስ ደስ ካላለን አላመንንም ማለት ነው፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ልብ #ምስጋና #ክብር #ማመን #ቃል #መናገር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ማሰላሰል #ማድረግ #ሁሉይቻላል #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment