Popular Posts

Friday, March 15, 2019

የማንቂያ ደውል


እግዚአብሄርን ለሚወዱ ሰዎች ነገር ሁሉ ለበጎ ይደረጋል፡፡
ለምሳሌ እግዚአብሄርን ስንፈልግ ሰው ቢበድለን በደሉ እኛን የሚጥለን ሳይሆን የሚያነቃን ደውላችን ነው፡፡  
ሰው ሲበድለን ስለበደለን ሰው እንድናውቅ እና እንድንረዳ የማንቂያ ደውል ነው፡፡
ሰው ሲበድለን ስለበደለን ሰው እንድናዝን እንድንራራ የማንቂያ ደውል ነው፡፡
ባይበድለን እንድንፀልይለት ትዝ የማይለን ሰው ቢበድለን ስለበደለን ሰው እንድንፀልይና እንድንማልድ የማንቂያ ደውል ነው፡፡
ባይረግመን ጊዜ ወስደን የማንባርከው ሰው ቢረግመን እንድንባርከው ስለእርሱ መልካም እንድድናስብ መልካም እንድንናገርና መልካም እንድናደርግ የማንቂያ ደውል ነው፡፡
እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ የማቴዎስ ወንጌል 5፡44
ሰዎች ሲበድሉን የእግዚአብሄርን መልካምነትና ልበ ሰፊነት ስንቱን እንደቻለ እንድናስብ የሚያደርግ የማንቂያ ደውል ነው፡፡
እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና። የማቴዎስ ወንጌል 5፡45
ሰዎች ሲበድሉን ያሉበትን የህይወት ሁኔታ ችግር ላይ መሆናቸውን ማወቅና አንድ ነገር ማድረግ አለብን፡፡ ሰዎች ሲበድሉን የእኛን ፀሎትና በረከት እንደሚያስፈልጋቸው የማንቂያ ደውሉን መስማትና መረዳት አለብን፡፡ የበደሉንን ሰዎች መልሰን ለመበደል ስንፈተን ይልቁንም በደሉን መልካም ለማድረግ እንደማንቂያ ደውል ልንጠቀምበት ይገባል፡፡
ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3፡9
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪ #ፀጋ #የሚያስችልሃይል #መልካም #ክፉ #አሸንፍ #ብቃት #የእግዚአብሄርችሎታ #የእግዚአብሄርሃይል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ፅድቅ #እግዚአብሄርንመምሰል #ራስንመግዛት #ልብ #ምስክርነት

No comments:

Post a Comment